ከ«ሳምሱ-ኢሉና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
|||
መስመር፡ 1፦
'''ሳምሱ-ኢሉና''' ከ1662 እስከ 1624 ዓክልበ. ድረስ ([[ኡልትራ አጭር]]) የ[[ባቢሎን]] 7ኛ ንጉሥ ነበረ። አባቱን [[ሃሙራቢ]]ን ተከተለው።
ለሳምሱ-ኢሉና ዘመን 38 ያህል የዓመት ስሞቹ ታውቀዋል። እንግዲህ በ9ኛው ዓመት (1654 ዓክልበ.) [[ካሳውያን]]ን እንዳሸነፈ ታውቋል። በሚከተለው ዓመት የ[[ላርሳ]] ገዥ [[2 ሪም-ሲን]] በዓመጽ ተነሣ፣ ይህም አመጽ በመላው ሱመርና አካድ ተስፋፋ። ሳምሱ-ኢሉና ግን እስከ 1649 ዓክልበ. ድረስ አመጸኖቹን ሁሉ አጠፋቸው። ከዚህ በኋላ ግን የ[[ኢሲን]] ገዥ [[ኢሉማ-ኢል]] በአመጽ ተነሣ፣ ደቡብም ሱመር በኢሊማ-ኢል ሥር «[[የባሕር-ምድር]]» የሚባለው ግዛት
በ፳ኛው አመት (1643 ዓክልበ.) [[ኤሽኑና]] እንደገና ባመጸ ጊዜ ሳምሱ-ኢሉና አመጹን አጠፋ። በ1635-34 ዓክልበ. ፪ [[አሞራውያን]] ነገሥታት ያዲሀቡምና ሙቲ-ሑርሻን አሸነፋቸው። በ1628 ዓክልበ. ደግሞ አሞራውያንን አሸነፋቸው።
|