ከ«የሂንዱ ሃይማኖት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
ጥNo edit summary |
||
መስመር፡ 3፦
የሂንዱ ሃይማኖት መንስኤ በ1500 አክልበ. ገደማ ወደ ሕንድ የወረሩት [[አርያኖች]] ነገዶች ያመኑበት በ[[ርግ ቬዳ]] የተገለጸው «[[ቬዲክ ሃይማኖት]]» ነበር። ይህ ቬዲክ ሃይማኖት ከኗሪዎቹ ከ[[ድራቪዲያን]] ብሔሮች እምነቶች ጋራ ሲቀላቀል አንድላይ የሂንዱ ሃይማኖት ሠርተዋል። ከዚህ የተነሣ ሁለቱ ጥንታዊ ልሳናታቸው [[ሳንስክሪት]]ና [[ታሚልኛ]] አንድላይ እንደ ቅዱሳን ወይም እንደ አማልክት ቋንቋዎች ይቆጠራሉ።
ሆኖም የሂንዱኢዝም ታሪክ ብዙ ተቃራኒ ፈሳሾች ያሉበት ወንዝ ይመስላል፤ በዚህም ወንዝ ውስጥ በብዙ ተቃራኒ ጣኦታት አማልክት የሚያምኑ ፈሳሾች አሉ፣ አማልክት ሁሉ የአንድያው ፈጣሪ አካላት ብቻ ናቸው የሚሉም ፈሳሾች፣ ምንም ነፍስ ወይም መንፈስ መኖሩን የሚክዱም ፈሳሾች ደግሞ ተገኝተዋል።
[[ስዕል:Kaliposter1940s.jpg|300px|thumb|በሂንዱ አፈ ታሪክ የሴት ጣኦት «[[ካሊ]]» ብዙ ጠላቶች በጦር ሜዳ ገድላ፣ ባልዋ [[ሺቫ]] ዓለሙን ሁሉ እንዳታጥፋ ፈርቶ በመንገድዋ ተኛ፤ ስህተቷንና ባሏ መሆኑን ዓውቃ ምላሷን በኅፍረት ዘረጋች።]]
[[ስዕል:Yajnavalkya and Janaka.jpg|
ከ700 ዓክልበ. ግድም ጀምሮ የ[[ሰምሳረ]] ትምህርት በሕንድ አገር በሰፊ ተቀበለ፤ እነዚህስ እምነቶች ሁሉ በሰምሳረ (ተመላሽ-ትስብዕት) ያምናሉ። እንደ «[[አብርሃማዊ ሃይማኖቶች]]» (በተለይ [[አይሁድና]]፣ [[ክርስትና]]፣ [[እስልምና]]) በ[[ሙታን ትንሳኤ]] ለ[[ፍርድ ቀን]] የሚያስተምሩ ሳይሆን፣ «ሰምሳረ» ማለት በእምነታቸው ከመሞት በኋላ ሕያዋን ዳግመኛ ከማሕጸን በተመላሽ ትስብዕት በመታየታቸው የሚሉ ናቸው። ይህን ትምህርት መጀመርያው የገለጸው ፈላስፋ [[ያጅኘቨልክየ]] የተባለው እንደ ነበር ይመስላል። በሂንዱኢዝም ደግሞ ኅብረተሠብ በአራት አጠቃላይ ወራሽ መደባት ወይም «[[ቫርና]]ዎች» ይከፈላል፤ እነርሱም [[ብራህሚን]] (ቄሳውንትና አስተማሮች)፣ [[ክሻትሪያ]] (ወታደሮችና ገዢዎች፣ ገበሬዎች)፤ [[ቫይስያ]] (ነጋዴዎች)ና [[ሹድራ]] (ሠራተኞች፣ አገልጋዮች) ናቸው።
|