ከ«አልፋቤት» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 2፦
'''አልፋቤት''' ማለት [[የዓለም ጽሕፈቶች]] ከተባሉት አምስት ዋና መደቦች አንዱ ነው። በአልፋቤቶች ውስጥ፣ እያንዳንዱ ምልክት ወይም ፊደል ባጠቃላይ ለተወሰነ ድምጽ ክፍል (እንደ ተነባቢ ወይም አናባቢ) ይወክላል።
 
ከአልፋቤቶች ቀድሞ በሆነ ዘዴ በ«[[ሎጎግራም]]» ጽሕፈት እያንዳንዱ ምልክት ለተለየ ቃል ወይም ክፍለ-ቃል ይወክላል፣ ለምሳሌ [[የቻይና ጽሕፈት]] ዛሬም እንዲህ ነው። እንዲሁም «[[ሲላቢክ]]» በሚባለው መደብ፣ እያንዳንዱ ምልክት የተለየ ክፍለ-ቃል ድምጽ ያሰማል፣ ለምሳሌ የ[[ጻላጊኛ]] ጽሕፈት፣ ወይም እንደ [[አቡጊዳ]] ወይም እንደ [[ሕንድ]] [[ብራሚክ ጽሕፈቶች]] ቤተሠብ፣ የክፍለ-ቃል ድምጽ ምልክቶች እንደ አነንባቢው ተመሳሳይ ናቸው። ስለዚህ «አልፋቤቶች» እንደ «ሎጎግራም» ወይም «ሲላቢክ» ሳይሆኑ ከነዚህ ሁሉ የተለዩ ናቸው።
 
ከሁሉ አስቀድሞ የተደረጁት አልፋቤቶች ከ[[ቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት]] ሲሆኑ ለአናባቢዎቹ የተለዩ ምልክቶች አልነበራቸውም፣ ስለዚህ የነዚህ አልፋቤት አይነት «[[አብጃድ]]» ነው። [[የፊንቄ አብጃድ]]፣ [[የዕብራይስጥ አብጃድ]]፣ [[የአረብኛ አብጃድ]]፣ [[የአረማይስጥ አብጃድ]] ወዘተ. ሁላቸው በዚህ አይነት ናቸው። ስያሜው «አብጃድ» ከ[[አረብኛ]] መጀመርያ ፊደል ስሞች [[አ]]፣ [[በ]]፣ [[ጀ]]፣ [[ደ]] መጣ። ከነዚህም ብዙዎች እንደ ዕብራይስትና አረብኛ አናባቢዎቹን በሌሎች ነጥቦች በኋላ አመለከቱ።