ከ«ባቢሎን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
ጥNo edit summary |
||
መስመር፡ 21፦
'''ባቢሎን''' ([[አካድኛ]]፦ ባቢሊ፣ [[ዕብራይስጥ]]፦ ባቤል) በ[[መስጴጦምያ]] የነበረ ጥንታዊ ከተማ ነው። ስሙ በአካድኛ ከ/ባብ/ (በር) እና /ኢሊ/ (አማልክት) ወይም «የአማልክት በር» ማለት ነበር። በዕብራይስጥ ግን ስሙ «ደባልቋል» እንደ ማለት ይመስላል (ዘፍ. 11:9)። «ባቢሎን» የሚለው አጠራር እንደ [[ግሪክኛ]]ው ነው።
መጀመርያው «ባቢሎን» የደቡብ [[ሱመር]] ከተማ የ[[ኤሪዱ]] መጠሪያ ስም እንደ ነበር ይመስላል። በ[[ሱመራውያን ነገሥታት ዝርዝር]] ዘንድ፣
ከሱመር ጽላቶች እንደምናውቅ፣ የኤሪዱ ግንብ ከተተወ በኋላ፣ የሱመር ዋና ከተማ (ዋና ቤተ መቅደስ የተገኘበት) ወደ [[ኒፑር]] ተዛወረ። ከዚያ ዘመን በኋላ የ[[አካድ]] ንጉሥ [[ታላቁ ሳርጎን]] (2070 ዓክልበ. ግድም) አዲስ የዋና መቅደስ ከተማ ወደ ስሜኑ ሠርቶ ማዕረጉን ከኒፑር አንዳዛወረ
ሆኖም ይህ የኒፑር ቅድምትነት መተካቱ ለጊዜው በሱመራውያን መካከል ተቃውሞ ያገኝ ነበር። ከአካዳውያን፣ [[ጉታውያን]]ና ሱመራውያን ገዥነት በኋላ፣ [[አሞራውያን]] የተባሉት ብሔር ወርሮ አያሌ ከተማ-ግዛቶች መሠረቱ። ከዚህም መካከል አንዱ [[ካዛሉ]] ሲሆን አሞራዊው አለቃ [[ሱሙ-አቡም]] በ1807 ዓክልበ. ግድም የባቢሎን ነጻነት ከካዛሉ አዋጀ፤ በዚያን ጊዜ እሱ የባቢሎን መጀመርያ ንጉሥ ሆነ። ከባቢሎን ነገሥታት [[ሃሙራቢ]] [[የሃሙራቢ ሕግ ፍትሕ]] ስለ መፍጠሩ በተለይ ይታወቃል። የባቢሎን መጀመርያ ውድቅት በ1507 ዓክልበ. በ[[ኬጥያውያን]] ንጉሥ [[፩ ሙርሲሊ]] እጅ ደረሰ። ከዚያ የኬጥያውያን ጓደኞች የነበሩት [[ካሣውያን]] ብሔር ባቢሎንን ገዛ፣ የከተማውም ስም በ[[ካሣኛ]] «'''ካራንዱኒያሽ'''» ተባለ። እነዚህ ካሣውያን እስከ 1163 ዓክልበ. ድረስ ባቢሎኒያን ገዙ።
|