ከ«የቅሌምንጦስ ስነ ጽሑፍ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 7፦
:«በ[[ይሁዳ]] ክፍላገር ውስጥ፣ ከዚሁ የ[[ሚያዝያ]] ወር ጀምሮ፣ ለ[[አይሁዶች]] ስለ [[እግዚአብሔር መንግሥት]] የሚያስተምር ፩ ሰው ይገኛል። የሚቀብሉትም የትዕዛዞቹን ደንቦችና ትምህርቱን መጠብቅ እንዳለባቸው እያለ ነው። ቃሉም በመለኰት እንደ ተመላና ለመታመን ተገቢ ሆኖ እንዲታመን፣ ብዙ ታላላቅ ሥራዎች፣ አስደናቂ ምልክቶችና ተዓምራት እንደሚሠራ ይባላል፤ ኃይሉም ከ[[እግዚአብሔር]] እንደሆነው ሁሉ፣ ደንቆሮች እንዲሰሙ፣ ዕውሮችም እንዲያዩ፣ መጻጒእ እንዲቆሙ እያደረገ፣ ከሰው ልጆች ዘንድ እያንዳንዱን ደዌና አጋንንትን ሁሉ ያስወጣ፤ አዎ፣ ስንኳ ያመጡለትን ሙትዓንን አስነሥቷል፤ ደግሞ ለምጻሞችን ከርቀት አይቶ ፈወሳቸው፤ የማይቻለውም ሥራ እንደሌለው ይባላል።»
 
በዚያው ዓመት ከይሁዳ ወደ ሮሜ የደረሰው ሰው ሁሉ እንዲህ አይነት ወሬ ስለ ደገመው፣ ኗሪዎቹምበተለይም በቅንነት እንጂ በጠማማነት እንዳልተናገሩ ስለ መሠላቸው፣ የሮሜ ኗሪዎች ከነቅሌምንጦስ እጅግ ሲገርሙ፣ በዓመቱም ውስጥ [[ባርናባስ]] የተባለው የኢየሱስ ደቀ መዝሙር በሮሜ ደርሶ በአደባባይ ስለክርስቶስ አዋጀ፣ እንዲህ ብሎ፦
 
:«ስሙኝ፣ እናንተ የሮሜ ዜጎች ሆይ። የእግዚአብሔር ልጅ አሁንም በይሁዳ ክፍላገር አለ፤ ለሚሰሙትም ሁሉ የዘለዓለማዊ ሕይወት ተስፋ ቃል ይሰጣል፤ ሆኖም ተግባሮቹን እንደ ላከውም፣ እሱም እግዚአብሔር አብ፣ ፈቃድ መሠረት ለማስተዳደር አስፈላጊ ይሆንበታል። ስለዚህ ከክፋት ወደ በጎነት፣ ከኅልፈታዊ ወደ ዘላቂው ዞራችሁ፣ አንድ አምላክ ብቻ፣ የሰማይና የምድር ገዥ መኖሩ፣ በጽድቅ ዓይኖቹ ፊት እናንተ ኃጥአን በዓለሙ መኖራችሁን፣ እወቁ። ብትቀይሩ ግን እንደ ፈቃዱም ብትሠሩ እንደ ሆነ፣ እንግዲህ ወደ መጪው ዓለም መጥታችሁ፣ ሕያዋን ሆናችሁ፣ የማይናገር በረከትና ዋጋ ታገኛላችሁ።»