ከ«ኤብላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 31፦
ከነዚህ ስሞች ብዙ በሃይማኖታዊ ሥነ ሥርዓቶቻቸው ደግሞ ይገኛሉ፣ በተለይም ከ«ሳጊሹ» እስከ «ኢሽሩድ-ዳሙ»፣ እና «ኤናር-ዳሙ» ያሉት ስሞች ይጠራሉ። ኢቢ-ዳሙ በ[[ካነሽ]] [[ሐቲ]] ከተገኘ ማኅተም ቅርስ ይታወቃል። ቁም-ዳሙ ከሌሎች ሰነዶች ሲታወቅ ከማሪ መንግሥት ጋራ የሆኑት ችግሮች በእርሱ ዘመን እንደ ጀመሩ ይመስላል። ይህም በማሪ ነገሥታት [[ሳዑሙ]] ወይም [[ኢቱፕ-ኢቫር]] ዘመናት እንደ ነበር ይታሥባል። ተከታዩም አዱብ-ዳሙ እጅግ አጭር ዘመን እንደ ነገሠ ይታወቃል።
 
የተገኙት መዝገቦች ከአዱብ-ዳሙ በኋላ ከገዙት ከሦስቱ መጨረሻ ነገሥታት ዘመኖች ናቸው። እነርሱም [[ኢግሪሽ-ሐላብ]] (12 ዓመታት)፣ [[ኢርካብ-ዳሙ]] (7 ዓመታት) እና [[ኢሻር-ዳሙ]] (35 ዓመታት) ናቸው (2127-2074 ዓክልበ.)። ከሃይለኛ ጠቅላይ ምኒስትሮቻቸው የሚታወቁ [[አራኩም]]፣ [[ኤብሪዩም]] እና [[ኢቢ-ዚኪር]] (ወይም ኢቢ-ሲፒሽ) ናቸው። መዝገቦቹ የተጻፉበት [[ኩኔይፎርም]] በተባለ ጽሕፈት ሲሆን ቋንቋቸው [[ኤብላኛ]] ነው፣ ይህ ለ[[አካድኛ]] ተመሳሳይ የሆነ [[ሴማዊ ቋንቋ]] ወይም ቀበሌኛ ነው።
 
ኢሻር -ዳሙ በማሪ ላይ ከ[[ናጋር]]ና ከ[[ኪሽ]] ጋራ ስምምነት ተዋዋለ፤ አለቃውም ኢቢ-ዚኪር የማሪን ሃያላት በ[[ተርቃ]] ውግያ አሸነፋቸው። ከዚህ በኋላ የኤብላ ሥራዊት [[አርሚ]]ን ያዙ፣ የኢቢ-ዚኪርም ልጅ ኤንዚ-ማሊክ እዝያ ገዥ ተደረገ። ኢሻር-ዳሙ ካረፈ በኋላ ግን ምናልባት 2074 ዓክልበ. ግ. ሳርጎን ወይም ማሪ ኤብላን እንዳጠፋ ይመስላል።