ከ«ገንዘብ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
መስመር፡ 9፦
[[ስዕል:BMC 06.jpg|thumb|left| ከክርስቶስ ልደበት በፊት በ640 ዓ.ዓ. ታትሞ የነበረው የመጀመሪያ ነው ተብሎ የሚታመነው የጥንቱ የ[[ልድያ]] አገር ሳንቲም]]
* የጥንቶቹ ሰወች እቃን በቃ በመለዋወጥ መገበያየት ቻሉ። ይህም በማይተዋወቁ ሰወች ዘንድ ነበር። በሚተዋወቁ ግን የስጦታ ልውውጥ ይደረግ ነበር።<ref>Graeber, David. 'Toward an Anthropological Theory of Value'. pp. 153-154.</ref>
* ቀስ ብሎ የተለያዩ ባህሎች [[ኮሞዲቲ ገንዘብ]] መጠቀም ጀመሩ። ከሁሉ አስቀድሞ [[ከብት]]ና [[እህል]] ([[ገብስ]]) መደበኛ ነበሩ። በተለይ [[ዛጎል]] በብዙ ህብረተሶቦች ዘንድ እንደ መገበባያ ገንዘብ ይጠቅም ነበር። <ref>Kramer, ''History Begins at Sumer'', pp. 52–55.</ref> [[መዳብ]]፣ [[ብረት]]፣ [[ብር (ብረታብረት)|ብር]]ና [[ወርቅ]] በክብደት ለመግዣ ቢጠቀሙም፣ ሰዎች ውዱን ብረትብረታበት ከርካሹ ጋራ ስላቀላቀሉት በአማካኝ ጥረቱ እየቀነሰ ሄደ።
* በ660 ዓክልበ. ያሕል ጥረቱን እንዲመረምሩ [[የፈተና ደንጊያ]] ዕውቀት ስላገኙ ለመጀመሪያ ጊዜ የ[[ወርቅ ሳንቲም]] እና የ[[ብር ሳንቲም]] መጠቀም የጀመሩት [[ልድያ|ልድያውያን]] ነበር።.<ref>Herodotus. ''Histories'', I, 94</ref> በኢትዮጵያም በ[[አክሱም]] ነገሥታት የታተሙ የወርቅ ሳንቲሞች ስራ ላይ ውለዋል።
* ከዚህ ቀጥሎ የተነሳው [[ተወካይ ገንዘብ]] የሚባለው ገንዘብ አመጣጡ እንዲህ ነው። ወርቅና ብር ነጋዴወች ለደንበኞቻቸው [[ደረሰኝ]] በመጻፍ፣ ያንን ደረሰኝ ደምበኞች በማምጣት በፈለጉት ሰዓት ወርቁንና ብሩን ማግኘት ቻሉ። ቀስ በቀስ ደረሰኙ በወርቁና በብሩ ቦታ ተተክቶ እንደ ሙሉ ገንዘብ መስራት ጀመረ። የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በ[[ሶንግ ስርወ መንግስት]] (970 ዓ.ም. - 1276 ዓ.ም.) ዘመን በ[[ቻይና]] አገር ነበር፣ ብሮቹም [[ያወዚ]] ይባሉ ነበር፣ አመጣጣቸውም ከላይ እንደተገለጸው የ[[ደረሰኝ]] ጽሁፈትን ተከትሎ ነው። [[አውሮጳ]] ውስጥ የወረቀት ገንዘብ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥቅም ላይ የዋለው በ1661፣ [[ስዊድን]] አገር ነበር። በዚህ ወቅት እያንዳንዱ ጥሬ የወረቀት ብር ወደ ተወሰነ የወርቅ ክብደት የሚቀየርበት ስሌት ነበረው።