ከ«ታላቁ ሳርጎን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
መስመር፡ 58፦
ወደ ምዕራብ ስላደረጉት ዘመቻዎች ሌሎች መዝገቦች ይታወቃሉ። በአንዳንድ ጽላት ዘንድ፣ ሳርጎን የ40 ሺህ ወታደሮች ሠራዊት ነበረው። ከሥራዊቱ ጋር [[ደብረ አማና]]ን ተሻገረ፣ ወደ አርዘ ሊባኖስ ደን ደረሱ። ወደ [[ማርዳማን]] አገር (ከስሜን [[ጤግሮስ]] ምዕራብ የነበረ የ[[ሆራውያን]] ክፍላገር) ለመውረር ያቅዳል። ከዚያ አገር የመጣ ተልእኮ ግን እንዲህ ይጠይቃል፦ «በዳርቻው ክፋቶች የሚያድቡበት የ[[አሞራውያን|አሙሩ]] አገር አይደለምን?» ነገር ግን ሳርጎን አይመልስም፣ የ[[ሲሙሩ]]ም ሰዎችና ከብቶች ሁሉ ይዘው ከተማውን አፈራረሰ። ይህ በስሜን መስጴጦምያ የተገኘ የሆራውያን ከተማ-አገር ነበር። አሙሩ እና [[ሱባርቱ]] አገሮች እንደ ያዙ ይላል።<ref>Joan Goodnick Westenholz, ''Legends of the Kings of Akkad: the Texts'', Text 6, 7.</ref>
በ[[ኬጥኛ]] የተጻፈው ግጥም ''የውግያ ንጉሥ'' ስለ ሳርጎን ምዕራብ ዘመቻ ነው። ይህ ጽሑፍ በአካድኛ ትርጉም ደግሞ በ[[አሦር]]ና በ[[አማርና ደብዳቤዎች]] መካከል (በ[[ግብጽ]]) ተገኝቷል። ሳርጎን በጥልቅ በ[[ሐቲ]] አገር ([[አናቶሊያ]]) እንደ ዘመተ ይናገራሉ። ጽሁፉ እንደሚተርከው፣ በሐቲ በ[[ካነሽ]] የኖሩት አካዳዊ ነጋዴዎች በ[[ቡሩሻንዳ]] ንጉሥ ኑርዳጋል ስለ ተበደሉ ሳርጎን በሩቅ መንገድ ከሠራዊቱ ጋር መጥቶ ኑርዳጋልን እንዲቀጣው በሚል
በአሦርኛው ''ሳርጎን ትውፊት'' እንደሚለው፣
|