ከ«መልከ ጼዴቅ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
ጥNo edit summary |
||
መስመር፡ 23፦
ከዚህ በላይ ከመጽሐፍ ቅዱስ ውጭ ስለ መልከ ጼዴቅ የተለያዩ ትምህርቶችና ታሪኮች አሉ።
*''[[ኪታብ አል-ማጋል]]'' በ[[ቅሌምንጦስ ሥነ ጽሑፍ]] ውስጥ ይመደባል። በዚህ ጹሑፍ ዘንድ፣ [[ሰብአ ሠገል]] ብራናውን ለክርስቶስ በሕጻንነቱ እንደ ስጦታ ሰጡት፣ እሱም ለ[[ጴጥሮስ]]፣ ጴጥሮስም ለተከታዩ ለሮሜ 2ኛው [[ፓፓ]] ለ[[ቅሌምንጦስ]] ያቀረበው ታሪክ ነው። በዚህ መሠረት፣ የመልከ ጼዴቅ አባት የ[[አርፋክስድ]] ልጅ ማሊኽ እንደ ነበር እናቱም ዮጻዳቅ እንደ ተባለች የአርፋክስድ አባት ሴም በጻፈው መዝገብ እንደ ተገኘ ይጨምራል። ከዚህ በላይ፣ በ[[ኖህ]] ትዕዛዝ ሴምና መልከ ጼዴቅ አብረው ወደ [[አራራት]] ሔደው የ[[አዳም]]ን ሬሳ ከ[[ኖህ መርከብ]] አወጡት። ከዚያ በሗላ፣ በመላዕክት ዕርዳታ ወደ ኢየሩስሌም ዞረው በ[[ጎልጎታ]] ኮረብታ ውስጥ አቀበሩት። አብራም በእግዚአብሔር ትዕዛዝ [[ይስሐቅ]]ን እንደ መሥዋዕት ወደ መሥዊያ ቦታ ባመጣው ጊዜ፣
ተመሳሳይ ዝርዝሮች ''[[የመዛግብት ዋሾ]]'' እና ''[[የአዳምና ሕይዋን ትግል ከሠይጣን ጋራ]]'' በተባሉት መጻሕፍት ይገኛሉ። በ''አዳምና ሕይዋን ትግል'' ዘንድ የመልከ ጼዴቅ አባት የ[[አርፋክስድ]] ልጅ [[ቃይንም]] ነው። ''[[መጽሐፈ ንቡ]]'' የሚባለው ጽሑፍ እንደሚለው የቃይንም 2 ልጆች ሻላሕ ([[ሳላ (የኤቦር አባት)|ሳላ]]) እና ማላሕ ሲሆኑ፣ ማላሕ ዮጻዳቅን አግብቶ የመልከ ጼዴቅ ወላጆች ሆኑ።
|