ከ«ኤንመርካር» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''ኤንመርካር''' በ[[ሱመር]] (ሳንጋር) ነገስታት ዝርዝር ዘንድ የ[[ኡሩክ]] (ኦሬክ) ከተማ መስራች ነበረ። በዚያ ዝርዝር ጽህፈት 420 (ወይም በሌላ ቅጂ 900) ዓመታት እንደ ነገሰ ይላል። ደግሞ አባቱ የ[[ኡቱ]] ልጅ [[መስኪያጝካሸር]] ወደ ባሕር ገብቶ ኤንመርካር መንግስቱን ከ[[ኤአና]] ከተማ እንዳመጣ ይጨምራል።
 
የኤንመርካር ስም በሌላ የሱመር ጽሑፍ ደግሞ ተገኝቷል። «''[[ኤንመርካርና የአራታ ንጉስ]]''» በተባለው ተረት እሱ የኡቱ ልጅ ይባላል። (ኡቱ በሱመር እምነት የ[[ጸሓይ]] አምላክ ነበር።) ይህ ተረት የሰው ልጅ ልሳናት መደባለቁን ይናገራል። ኡሩክን ከመመስረቱ በላይ ታላቅ መስጊድ በ[[ኤሪዱ]]ም እንዳሰራ ይተረታል። ለመሆኑም፣ [[አራታ]] እንዲገዛለት የሚለው መልእክት በአፍ መናገር ስለሚከብድ፣ ኤንመርካር ጽሕፈት በሸክላ ጽላት ላይ መጻፍ እንደ ፈጠረ ይላል።
 
በተጨማሪ በዚሁ ጽሑፍ ኤንመርካር የዙሪያው አገሮች ልዩ ልዩ ልሳናት እንደገና አንድ እንዲሆኑ ይጸልያል። እነዚህ አገራት [[ሹቡር]]፣ [[ሐማዚ]]፣ [[ሱመር]]፣ ኡሪ-ኪ (የ[[አካድ]] ዙርያ) እና [[አሞራውያን|የማርቱ አገር]] ናቸው።