ከ«ሥልጣኔና እንጉርጉሮው» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
መስመር፡ 5፦
ግለሰቦች በስልጣኔ ላይ ያንጎራጉራሉ የዚህ ምክንያቱ በአንድ ግለሰብና በስልጣኔ መካከል የማያባራ ቅራኔ በመኖሩ መሆኑን ፍሩድ አሰፈረ። የዚህ ቅራኔ መሰረታዊ መንሴ ግለሰቦች በደመነፍስ ነጻነትን ሲፈልጉ ስልጣኔ ግን ከያንዳንዱ ግለሰብ መታዘዝንና እራስን መግዛት ይጠይቃል። የሰው ልጅ በራሱ አረመኒያዊ የሆኑ የደመነፍስ ፍላጎቶች አሉት (ለምሳሌ የመግደል፣ የማያልቅ የፍትወተ ስጋ ፍላጎት ወዘተ...) ። ነገር ግን እኒህ ደመነፍስ ፍላጎቶች በማህበራዊ ኑሮ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳሉ። ስለሆነም በማናችውም የታሪክ ዘመናት የተፈጠሩ ስልጣኔወች የሰውን ልጅ ደመነፍስ ፍላጎት ለማቀብ ህግ አውጥተዋል። አትግደል፣ አትድፈር፣ አታመንዝር፣ የሌላ ሰውን ሃብት አትውሰድ ወዘተ... የሚሉ ህጎች ወጥተው ህጎቹን የተላለፈ ከፍተኛ ቅጣት በዘመናትና በስልጣኔያት ሁሉ ሲቀጣ ይታያል። ይህ እንግዲህ፣ በፍሩድ አስተሳሰብ፣ በስልጣኔ ውስጥ የሚንሸራሽሩ ዜጎች በስልጣኔ ላይ የማያባራ ቅሬታ እንዲያበጁ አድርጓል።
 
ከላይ የተጻፈው የፍሩድ ርዕዮተ አለም መሰረቱ የሰው ልጅ አንድ አንድ በተፈጥሮ ያሉት ምንጊዜም የማይቀየሩ የደመነፍስ ባህርዮች ናቸው። ከነዚህ የሰው ልጅ መሰረታዊ ባህርዮች ፍሩድ ዋና ያላቸው፦ ፍትወተ ስጋ የመፈለግ ባህርይና አንድ ግለሰብ ይህን ፍላጎት እንዳያሟላ ከላይ ሆነው የሚከለክሉትን የበላዮች (ባለ ስልጣናት፣ አለቆች፣ አዛዦች..ወዘተ..)ና በፍትወት ስጋ ተፎካካሪወች ላይ ጥል ለመፍጠር ያለ የደመነፍስ ባህርይ ናቸው።
 
===መጽሃፉ ባጭሩ===
ፍሩድ መጽሃፉን የሚጀመረው የሃይማኖታዊነትን ስሜት መነሻ መነሻ ሊሆን ይችላል ያለውን የ[[ውቅያኖሳዊ ስሜት]]ን መነሻ በመመርመር ነው። ውቅያኖሳዊ ስሜት የሚለው ጽንሰ ሃሳብ አንድ ግለስብ በአንድ ወቅት ምሉዕነት፣ ወሰን አልባነትና ዘላለማዊነትን በህሊናው ሲቀርጽ ወይም በጥልቅ እንዲሰማው ሲሆን ነው። ፍሩድ ይህን "በአለም ውስጥ እንደጨው የመሟሟት" ስሜት በግሉ ሊሰማው ባይችልም ሌሎች ግለሰቦች በጤናማ እና በታወከ አይምሮ ሊሰማቸው እንደሚችል አስተውሏል። ለምሳሌ ሰወች [[ፍቅር]] ሲይዛቸው በ[[እኔነት]]ና በሚወደደው ውጫዊ ነገር መካከል ያለው ድንበር ወይ ይደበዝዛል፣ ወይ ይቆራረጣል ወይም ደምጎ ሟሙቶ ይጠፋል። ስለዚህም ለፍሩድ የ[[ውቅያኖሳዊ ስሜት]] የሚመነጨው ቀደምት የሰወች ንቃተ ህሊና እኔነቱን ከከባቢው አለም ሳይለይ በፊት ሁሉ በሁሉ በተደባለቀበት ኩነት ሲገኝ የሚፈጠር ስሜት ነው። ይህም ከፍሩድ አጠቃላይ እምነት ጋር የተያያዘ ነው፣ ይሄውም የ[[ሃይማኖታዊ ስሜት]] የሚመነጨው [[ጨቅላ|ጨቅላወች]] ከሚሰማቸው ደካማነትና እራስን አለመቻል የተነሳ "የአባታቸውን እርዳታ ከመፈለግ" የሚመነጭ ነው <ref> Strachey 2001, pg. 72 </ref>፤ ስለሆነም በፍሩድ አስተያየት "የውቅያኖሳዊ ስሜት በኋላ ከሃይማኖት ጋር ተያያዘ"። በሌላ አባባል እውነተኛ የሃይማኖት ስሜት ሳይሆን ነገር ግን ይህን ሁኔታ የተሰማቸው ሰወች እንደ እውነተኛ የሃይማኖት ስሜት ያዩታል።
 
{{መዋቅር}}