ከ«ሠርፀ ድንግል» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «አፄ '''ሠርጸ ድንግል''' ( 1550 - 4 ጥቅምት 1597 እ.ኤ.አ) ) በዙፋን ስማቸው "መልአክ ሰገድ'' የኢትዮጵያ ንጉ...»
 
ሎሌ መጨመር: en:Sarsa Dengel; cosmetic changes
መስመር፡ 1፦
አፄ '''ሠርጸ ድንግል''' ( [[1550]] - 4 ጥቅምት 1597 እ.ኤ.አ) ) በዙፋን ስማቸው "መልአክ ሰገድ'' የኢትዮጵያ ንጉስ ሲሆኑ የነገሱበትም ዘመን (1563 - 1597 እ.ኤ.አ ) ነበር። የኒህ ንጉስ አባት አጼ [[ሚናስ]] ሲሆኑ እናታቸው ደግሞ [[አድማስ ሞገሴ]] በምባል ይታወቃሉ።
 
ሠርጸ ድንግል ወደስልጣን የወጣው በ[[ሸዋ]] ውስጥ ይገኙ የነበር የጦር መሪወች ምርጫ በማካሄድና ብሎም "እናት ንግስት" ተብላ ትታወቅ የነበርችው የሃዲያዋ [[ንግስት እሌኒ]] በማጽደቋ ነበር። ይህ ከሆነ በኋላ [[ባህር ንጉስ]] [[ይስሃቅ]] የተባለው ያሁኑ [[ኤርትራ]] መሪ በአጼ ሚናስ ዘመን ያመጸ ቢሆንም ልጁ ሲነግስ የልጁን ስልጣን ተቀበለ። ይሁንና ሰርጸ ድንግል ሙሉ ሰላም ኑሮት አገሪቱን አላስተዳደርም ። ምሳሌ የራሱ ያጎት ልጅ የሆነው [[ሐመልማል]] በ1563 ፣ ክሁለት አመት በኋል ፋሲል የተባለው ያጎቱ ልጅ አመጽ አስነስተውብታል። ከዚያም [[ይስሃቅም]] በ[[ኦቶማን]] ቱርኮች ታግዞ አመጽ ማስነሳቱ አልቀረም። በዚህ ጊዜ ንጉሱ ወደ [[ትግራይ]] በመዝመት በ1576 ባህረ ነጋሹንና አባሪ ኦቶማኑን [[ኦዝደሚር ፓሻ]]ንና ሱልጣን [[መሃመድ የሃረሩ አራተኛ]] የተባሉትን በጦርነት አሸንፎ ገደላቸው። ከ12 አመት በሁዋላ በ1588 የኦቶማን ቱርኮች ወደ ውስጥ ዘልቀው ባሁኑ [[ኤርትራ]] የሚገኘውን [[ደባርዋ]]ን ሊቆጣጠሩ ሲሞክሩ [[አርቂቆ]] ላይ የነበረውን የቱርኮች ግዛት በሚቀጥለው አመት አፈረሰባቸው።
 
ሰርጸ ድንግል የኖረበት ዘመን ከ[[ግራኝ አህመድ]] ወረራ ጥቂት ዘመን አሳልፎ ስለነበር የህዝቦች ፍልሰት በዚሁ ዘመን ይታይ ነበር። የኦሮሞን ወደ ሰሜን ወረራ ለመጀመሪያ ጊዜ የተጋፈጠ ንጉስ ይሄው ሰርጸ ድንግል ነው። በዚሁ ዘመን የኦሮሞወች ጥንካሬ ከማየሉ የተነሳ [[ኑር ኢብን ሙጃሂድ]] የተሰኘውን የግራኝ ምትክ በመግደል [[ሐረር]]ን ወረው ነበር። ቀጥሎም ወደሰሜን በመዝመት ሰርጸ ድንግል በነገሰ በ10ኛው አመት [[ዝዋይ ሃይቅ]] አካባቢ ከንጉሱ ሰራዊት ጋር ተጋጭተው ተሸነፉ። ከዚህ በኋላ ንጉሱ በኦሮሞወች ቡድኖች ላይ በ1578 እና በ1588 ዘምቷል።
 
በ1580 እና 85 ደግሞ በ[[ቤተ እስራኤል]] ([[ፈላሾች]]) ላይ ዘምቷአል። [[አገው]] ላይም በ1581 እና 85፣ [[ጋምቦ]] ላይ በ 1590 አድርጓል። [[እንራያ]] ደግሞ ሁለት ጊዜ በ 1586 እና 97 ጦርነት ከፍቷል። ስለመጨረሻው ዘመቻው የንጉሱ ዜና-መዋዕል <ref> በፕሮፌሰር [[ፓንክረስት]] የተተረጎመ "The Ethiopian Royal Chronicles''. Addis Ababa: Oxford University Press, 1967.</ref> እንዲህ ሲል ያትታል፡
: መነኮሳት ተሰብስበው ንጉሱ ወደጦር ሜዳ እንዳይሄድ ለመኑት፣ ንጉሱም ግን ልቡ እንደደነደነ ስለተገነዘቡ በተወሰነ ወንዝ ውስጥ የሚገኝን አሳ እንዳይበላ አጥብቀው አስጠነቀቁት። እሱ ግን የተባለውን ቸል በማለት ባስጠነቀቁት ወንዝ ሲያልፍ ከዚይ ወንዝ የወጣን አሳ በላ። ሳይዘገይም በጸና ታመመና ሞተ። <ref>G.W.B. Huntingford, ''Historical Geography of Ethiopia'' (London: British Academy, 1989), p.149.</ref>
 
በሞተም ጊዜ [[ሬማ]] ደሴት፣ [[ጣና ሃይቅ]]፣ [[መድሃኔ አለም]] ቤ/ክርስቲያን ተቀበረ። <ref>R.E. Cheesman, [http://www.jstor.org/stable/1785868 "Lake Tana and Its Islands", ''Geographical Journal''], 85 (1935), p. 498</ref>
 
== ማጣቀሻወች ==
<references/>
 
{{የኢትዮጵያ ነገሥታት}}
[[መደብ: የኢትዮጵያ ታሪክ]]
 
 
[[መደብ: የኢትዮጵያ ታሪክ]]
 
[[de:Sarsa Dengel]]
[[en:Sarsa Dengel]]
[[fr:Sarsa Dengel d'Ethiopie]]
[[he:סרצה דנגל, קיסר אתיופיה]]