ከ«ናርመር» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 2፦
'''ናርመር''' ለ[[ሥነ ቅርስ]] የሚታወቅ [[የግብጽ ቀድሞ ዘመን መንግሥት]] ፈርዖን ነበረ። ስሙ በ[[ግብጽ ሃይሮግሊፍ]] ሲጻፍ፣ የ[[አምባዛ]] (አስቀያሚ የባሕር [[አሳ]] ወይም በ[[ግብጽኛ]] «ናር») ከ[[መሮ]] (በግብጽኛ «መር») በላይ ነው። ከ[[ሔሩ]] (ወይም ሆሩስ፣ ሖር) ወገን በመሆኑ ስሙ በሙሉ «ሔሩ ናርመር» (ወይም ምናልባት «ሔሩ መር-ናር») ነበረ።
 
[[የናርመር ዱላ]] የተባለው ቅርስ በዙፋን ሲቀመጥ የታችኛ (ስሜኑ) ግብጽ ዘውድ በራኡበራሱ ላይ ሲጫን ያሳያል። ሀርሱ ዙሪያ የሚያገልግሉ ሰዎች አሉ። በላይኛው ተርታ አጫጭር ሰዎች ዓላማዎች ሲሸክሙ አንዱ «[[ሴት (ግብፅ)|ሴት]]» ምልክት ([[አዋልደጌስ]] ወይም [[ቀበሮ]])፣ አንዱም የ[[ጊንጥ]] ምልክት፣ ሁለቱም የሔሩ ምልክት ([[ጭላት]]) አለባቸው።
 
በ[[1890]] ዓ.ም. በተገኘው [[የናርመር መኳያ ሠሌዳ]] በተባለው ቅርስ ላይ የናርመር መልክ በሁለቱ ገጾች ላይ ይታያል። በፊተኛው ገጽ ላይ የታችኛ ግብጽ ዘውድ (ቀዩ ዘውድ)፤ በጀርባውም ላይ የላይኛ ግብጽ ዘውድ (ነጩ ዘውድ) በራሱ ላይ ይታያል። ስለዚህ ሁለቱ ክፍሎች መጀመርያው ያዋሐደው ፈርዖን በተለመደው ታሪክ [[ሜኒስ]] ሲሆን፣ እርሱና ናርመር አንድ እንደ ነበሩ በሰፊ ይታመናል።