ከ«የጊንጥ ዱላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «thumb|320px|በዱላው የታየው ትርዒት '''የጊንጥ ዱላ''' የግብጽ ጥንታዊ መንግሥት ቅርስ ሲ...» |
oops, correct own typo - CS |
||
መስመር፡ 2፦
'''የጊንጥ ዱላ''' [[የግብጽ ጥንታዊ መንግሥት]] ቅርስ ሲሆን በ[[ነቀን]] (ሄራኮንፖሊስ) ከተማ የተገኘ ስብብር የዱላ ራስ ነው። ከበሀ ድንጋይ ተሠራ። በትልቁ ክፍል የተቀረጸው ትርዒት [[ንጉሥ ጊንጥ]] ስለሚያሳይ፣ ቅርሱ «የጊንጥ ዱላ» ተብሏል።
ይህ «ንጉሥ ጊንጥ» ከፈርዖኖች ዘመን አስቀድሞ በግብጽ የነገሠ አለቃ መሆኑ ይታወቃል። ጥንታዊው መንግሥት በ«[[ሔሩ]] ወገን» እንደ ተመሠረተ ሁሉ፣ ዱላው በአረመኔው አምላክ በሔሩ ቤተ መቅደስ ፍርስራሽ በ[[1890]] ዓ.ም. ተገኝቶ ነበር። በተቀረጸው ትርዒት፣ አለቃው ከሰው ረጅም ሆኖ ማረሻም ይዞ በራሱ ላይ «የላይኛ ግብጽ ነጭ ዘውድ» አለበት። አጠገቡ የ[[ጊንጥ]]
አለቃውን የሚያገልግሉት ሰዎች በመነጻጸር በጣም አጭር ሆነው ያሳያል። ከሱም በላይ የዓላማዎች ተርታ ሊታይ ይችላል። ከነዚህ ሁለቱ ዓላማዎች «የሴት ወገን» ምልክት እሱም «የሴት እንስሳ» ([[አዋልደጌሳ]] ወይም [[ቀበሮ]]) አለባቸው። ከየአላማው ደግሞ እንደ ወፍ የሚመስል ፍጡር በአንገት ይሰቀላል። የዚህ ትርዒት ትርጉም በእርግጥ ባይታወቅም፣ በጥንታዊ ግብጽ ለመግዛት የተነሡት ወገኖች ታሪክ እንደሚነካ ይገመታል።
|