ከ«የጊንጥ ዱላ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አዲስ ገጽ ፈጠረ፦ «thumb|320px|በዱላው የታየው ትርዒት '''የጊንጥ ዱላ''' የግብጽ ጥንታዊ መንግሥት ቅርስ ሲ...»
 
oops, correct own typo - CS
መስመር፡ 2፦
'''የጊንጥ ዱላ''' [[የግብጽ ጥንታዊ መንግሥት]] ቅርስ ሲሆን በ[[ነቀን]] (ሄራኮንፖሊስ) ከተማ የተገኘ ስብብር የዱላ ራስ ነው። ከበሀ ድንጋይ ተሠራ። በትልቁ ክፍል የተቀረጸው ትርዒት [[ንጉሥ ጊንጥ]] ስለሚያሳይ፣ ቅርሱ «የጊንጥ ዱላ» ተብሏል።
 
ይህ «ንጉሥ ጊንጥ» ከፈርዖኖች ዘመን አስቀድሞ በግብጽ የነገሠ አለቃ መሆኑ ይታወቃል። ጥንታዊው መንግሥት በ«[[ሔሩ]] ወገን» እንደ ተመሠረተ ሁሉ፣ ዱላው በአረመኔው አምላክ በሔሩ ቤተ መቅደስ ፍርስራሽ በ[[1890]] ዓ.ም. ተገኝቶ ነበር። በተቀረጸው ትርዒት፣ አለቃው ከሰው ረጅም ሆኖ ማረሻም ይዞ በራሱ ላይ «የላይኛ ግብጽ ነጭ ዘውድ» አለበት። አጠገቡ የ[[ጊንጥ]] መልዕክትምልክት አለ፤ የዚሁ ቃል ግብጽኛ አጠራር ግን እርግጠኛ ስለማይሆን፣ ዛሬ የአለቃው ስም «ንጉሥ ጊንጥ» ብቻ ይባላል።
 
አለቃውን የሚያገልግሉት ሰዎች በመነጻጸር በጣም አጭር ሆነው ያሳያል። ከሱም በላይ የዓላማዎች ተርታ ሊታይ ይችላል። ከነዚህ ሁለቱ ዓላማዎች «የሴት ወገን» ምልክት እሱም «የሴት እንስሳ» ([[አዋልደጌሳ]] ወይም [[ቀበሮ]]) አለባቸው። ከየአላማው ደግሞ እንደ ወፍ የሚመስል ፍጡር በአንገት ይሰቀላል። የዚህ ትርዒት ትርጉም በእርግጥ ባይታወቅም፣ በጥንታዊ ግብጽ ለመግዛት የተነሡት ወገኖች ታሪክ እንደሚነካ ይገመታል።