አጼ '''ጅን አሰገድ''' የአጼ [[ይግባ ጽዮን]] ልጅ የአጼ[[ይኩኖ አምላክ]] የልጅ ልጅ ሲሆኑ ከ1297-1298 ለአንድ አመት የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ታሪክ ጻህፍት እንደሚሉት አባታቸው ይግባ ጽዮን 5 ወንድ ልጆች ስለነበሩዋቸውና የትኛው ንጉስ እንዲሆን መምረጥ ስላልቻሉ እያንዳንዱ ወንድ ልጅ አንድ አንድ አመት እንዲነግስ ቃል ስላስገቡዋቸው 1 አመት ብቻ ነግሰዋል<ref>Paul B. Henze, ''Layers of Time, A History of Ethiopia'' (New York: Palgrave, 2000), p. 60.</ref> <ref>ታደሰ ታምራት, ''Church and State in Ethiopia'' (Oxford: Clarendon Press, 1972), p. 72.</ref>
[[ዋሊስ በድጅ]] የተሰኘው የታሪክ ተመራማሪ ተፎካካሪ የንጉሳዊ ቤተሰቦችን [[አምባ ግሸን]] ማሰር የጀመሩት እኒሁ ንጉስ ናቸው ይላል። ይህንም ያደረጉት አስቸጋሪ ወንድማቸውን [[ሳባ ሰገድ]]ን ከራሳቸው ለማራቅ ነበር ይላል ዋሊስ። ከሳባ ሰገድ በተጨማሪ ሶስቱ ወንድሞቻቸውንና የራሳቸውን ልጅ አምባው ላይ እንዳሰሩ ዋሊስ ያትታል።<ref>E. A. Walis Budge, ''A History of Ethiopia: Nubia and Abyssinia'', 1928 (Oosterhout, the Netherlands: Anthropological Publications, 1970), p. 287. According to G.W.B Huntingford, this information comes from the Jesuit historian [[Pedro Páez]], who was told this story by Emperor [[Susenyos of Ethiopia|Susenyos]] (''The Historical Geography of Ethiopia'' [London: The British Academy, 1989], p. 75).</ref>