ከ«ሥርዓተ ነጥቦች» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
Amharic punctuation Marks Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit Android app edit |
ቁ Tags: Reverted Visual edit |
||
መስመር፡ 1፦
'''አማርኛ ፦ ሥርዓተ ነጥቦች'''
ብዙዎቻችን ከሁለት ነጥብና ከአራት ነጥብ በስተቀር ሌሎቹን ሥርዓተ - ነጥቦች በሚገባ አንጠቀምም። ለምሣሌ አንዱ ድርብ ሠረዝ (፤) የሚጠቀምበትን ቦታ ሌላው ነጠላ ሠረዝ (፣)/(፥) ይጠቀማል፤ እንዲሁም አንዱ ትእምርተ - ጥያቄ (?) የሚጠቀምበትን ቦታ ሌላው ትእምርተ - አንክሮን (!) ይጠቀማል። ወጥ የሆነ የአጠቃቀም ስርዓት አይታይም። በርግጥ አንዳንዴ ድርብ ሠረዝን መጠቀም አለመጠቀም የምርጫ ጉዳይ ሊሆን ይችላል። ሐሳቦች ተደራርበው ወይም ተጣምረው እንዲቀርቡ የፈለገ ሰው ድርብ ሠረዝን ተጠቅሞ ሐሳቦቹን በአንድ ዐረፍተ ነገር ሊያጠቃልል ይችላል። በአንጻሩ ደግሞ ሐሳቦቹን ቆራርጦ የተለያዩ ዐረፍተ ነገሮች በማድረግ ለየብቻቸው ሊያቀርብ የፈለገ ሰው አራት ነጥብን መጠቀም ይችላል። ዞሮ ዞሮ የሥርዓተ - ነጥቦችን አጠቃቀም ማወቅ ተገቢ ነው።
|