ከ«ሥርዓተ ነጥቦች» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
Amharic punctuation Marks
Tags: በንፋስ ስልክ Mobile app edit Android app edit
Tags: Reverted Visual edit
መስመር፡ 1፦
'''አማርኛ ፦ ሥርዓተ ነጥቦች'''
 
በወረቀትጇበወረቀት ላይ የሰፈረ ሐሳብ (ቋንቋ) መልእክቱ ግልጽ ሆኖ እንዲተላለፍ ሥርዓተ - ነጥቦች የጎላ ድርሻ አላቸው። በጽሑፍ ላይ ነጥቦችን አስተካክሎ ካለመጠቀም የተነሳ ዐረፍተ ነገሮችን ያሻማሉ፤ መልእክቶች ይዛባሉ፤ ሐሳቦች ይድበሰበሳሉ። ስለዚህ ሐሳቦችን ግልጽ በሆነ መልኩ በጽሑፍ ለማስተላለፍም ሆነ የተጻፈውን መልእክት በትክክል አንብቦ ለመረዳት ሥርዓተ - ነጥቦችን እና አገልግሎታቸውን በሚገባ ማወቅ ተገቢ ይሆናል።
 
ብዙዎቻችን ከሁለት ነጥብና ከአራት ነጥብ በስተቀር ሌሎቹን ሥርዓተ - ነጥቦች በሚገባ አንጠቀምም። ለምሣሌ አንዱ ድርብ ሠረዝ (፤) የሚጠቀምበትን ቦታ ሌላው ነጠላ ሠረዝ (፣)/(፥) ይጠቀማል፤ እንዲሁም አንዱ ትእምርተ - ጥያቄ (?) የሚጠቀምበትን ቦታ ሌላው ትእምርተ - አንክሮን (!) ይጠቀማል። ወጥ የሆነ የአጠቃቀም ስርዓት አይታይም። በርግጥ አንዳንዴ ድርብ ሠረዝን መጠቀም አለመጠቀም የምርጫ ጉዳይ ሊሆን ይችላል። ሐሳቦች ተደራርበው ወይም ተጣምረው እንዲቀርቡ የፈለገ ሰው ድርብ ሠረዝን ተጠቅሞ ሐሳቦቹን በአንድ ዐረፍተ ነገር ሊያጠቃልል ይችላል። በአንጻሩ ደግሞ ሐሳቦቹን ቆራርጦ የተለያዩ ዐረፍተ ነገሮች በማድረግ ለየብቻቸው ሊያቀርብ የፈለገ ሰው አራት ነጥብን መጠቀም ይችላል። ዞሮ ዞሮ የሥርዓተ - ነጥቦችን አጠቃቀም ማወቅ ተገቢ ነው።