ቁርአን ላይ ስሞች


በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው

ይህንን አስቂኙ ጥያቄ ብየዋለሁ ብዙ #የዋህ ክርስቲያኖች <ቁርአን ላይ የ አልመሲህ ኢሳ ስም 25 ጊዜ ሲጠቀስ የሙሃመድ ስም ግን 4 ጊዜ ብቻ ነው የተጠቀሰው > ያላሉ መጀመሪያ ስም ቁጥር መበላለጥ በስልጣንና በደረጃ ላይ ምንም ለውጥ አያመጣም ወገኖቻቺን ይህን ያህል ተጠቃሷል ከማለታቸው በፊት ምንምን ነው ያለው ብለው አይመረምሩም አላህ ኢሳ [አለይሂሰላም]ን 25 ጊዜ ቢጠቅሰውም እኮ ባርያና መልእክተኛ የተፈጠረ እያለ እንጂ አምላክ እያለ አደለም የሚጠራው ለናሙና ያህል 5፥75 < مَّا ٱلْمَسِيحُ ٱبْنُ مَرْيَمَ إِلَّا رَسُولٌۭ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ ٱلرُّسُلُ وَأُمُّهُۥ صِدِّيقَةٌۭ ۖ كَانَا يَأْكُلَانِ ٱلطَّعَامَ ۗ ٱنظُرْ كَيْفَ نُبَيِّنُ لَهُمُ ٱلْـَٔايَٰتِ ثُمَّ ٱنظُرْ أَنَّىٰ يُؤْفَكُونَ የመርየም ልጅ አልመሲሕ ከበፊቱ መልክተኞች በእርግጥ ያለፉ የኾነ መልክተኛ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡ እናቱም በጣም እውነተኛ ናት፡፡ (ሁለቱም) ምግብን የሚበሉ ነበሩ፤ አንቀጾችን ለነርሱ (ለከሓዲዎች) እንዴት እንደምናብራራ ተመልከት ከዚያም (ከእውነት) እንዴት እንደሚመለሱ ተመልከት፡፡>

3፥59< إِنَّ مَثَلَ عِيسَىٰ عِندَ ٱللَّهِ كَمَثَلِ ءَادَمَ ۖ خَلَقَهُۥ مِن تُرَابٍۢ ثُمَّ قَالَ لَهُۥ كُن فَيَكُونُ አላህ ዘንድ የዒሳ ምሳሌ እንደ አዳም ብጤ ነው፡፡ ከዐፈር ፈጠረው፡፡ ከዚያም ለርሱ (ሰው) «ኹን» አለው፤ ኾነም፡፡>

4፥172< لَّن يَسْتَنكِفَ ٱلْمَسِيحُ أَن يَكُونَ عَبْدًۭا لِّلَّهِ وَلَا ٱلْمَلَٰٓئِكَةُ ٱلْمُقَرَّبُونَ ۚ وَمَن يَسْتَنكِفْ عَنْ عِبَادَتِهِۦ وَيَسْتَكْبِرْ فَسَيَحْشُرُهُمْ إِلَيْهِ جَمِيعًۭا አልመሲሕ (ኢየሱስ) ለአላህ ባሪያ ከመኾን ፈጽሞ አይጠየፍም፡፡ ቀራቢዎች የኾኑት መላእክትም (አይጠየፉም)፡፡ እርሱን ከመገዛት የሚጠየፍና የሚኮራም ሰው (አላህ) ሁሉንም ወደ እርሱ በእርግጥ ይሰበስባቸዋል፡፡>

4፥163< ۞ إِنَّآ أَوْحَيْنَآ إِلَيْكَ كَمَآ أَوْحَيْنَآ إِلَىٰ نُوحٍۢ وَٱلنَّبِيِّـۧنَ مِنۢ بَعْدِهِۦ ۚ وَأَوْحَيْنَآ إِلَىٰٓ إِبْرَٰهِيمَ وَإِسْمَٰعِيلَ وَإِسْحَٰقَ وَيَعْقُوبَ وَٱلْأَسْبَاطِ وَعِيسَىٰ وَأَيُّوبَ وَيُونُسَ وَهَٰرُونَ وَسُلَيْمَٰنَ ۚ وَءَاتَيْنَا دَاوُۥدَ زَبُورًۭا እኛ ወደ ኑሕና ከርሱ በኋላ ወደ ነበሩት ነቢያት እንዳወረድን ወደ አንተም አወረድን፡፡ ወደ ኢብራሂምም፣ ወደ ኢስማዒልም፣ ወደ ኢስሓቅም፣ ወደ ያዕቆብም፣ ወደ ነገዶቹም፣ ወደ ዒሳም፣ ወደ አዩብም፣ ወደ ዩኑስም፣ ወደ ሃሩንና፣ ወደ ሱለይማንም አወረድን፡፡ ለዳውድም ዘቡርን ሰጠነው፡፡>

እኒህና የመሳሰሉት አንቀጻት ኢሳ [እየሱስን] ባርያና መልእክተኛ እንጂ አምላክ አይለውም በቁጥር መብዝት ቢሆንማ ሰይጣን እኮ ከኢሳ ይልቅ 88 ጊዜ ተጠቅሷል ለናሙና ያህል

24፥21< ۞ يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُوا۟ لَا تَتَّبِعُوا۟ خُطُوَٰتِ ٱلشَّيْطَٰنِ ۚ وَمَن يَتَّبِعْ خُطُوَٰتِ ٱلشَّيْطَٰنِ فَإِنَّهُۥ يَأْمُرُ بِٱلْفَحْشَآءِ وَٱلْمُنكَرِ ۚ وَلَوْلَا فَضْلُ ٱللَّهِ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَتُهُۥ مَا زَكَىٰ مِنكُم مِّنْ أَحَدٍ أَبَدًۭا وَلَٰكِنَّ ٱللَّهَ يُزَكِّى مَن يَشَآءُ ۗ وَٱللَّهُ سَمِيعٌ عَلِيمٌۭ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! የሰይጣንን እርምጃዎች አትከተሉ፡፡ የሰይጣንንም እርምጃዎች የሚከተል ሰው (ኀጢአትን ተሸከመ)፡፡ እርሱ በመጥፎና በሚጠላ ነገር ያዛልና፡፡ በእናንተም ላይ የአላህ ችሮታና እዝነቱ ባልነበረ ኖሮ ከናንተ አንድም ፈጽሞ ባልጠራ ነበር፡፡ ግን አላህ የሚሻውን ሰው ያጠራል፡፡ አላህም ሰሚ ዐዋቂ ነው፡፡>

5፥91< إِنَّمَا يُرِيدُ ٱلشَّيْطَٰنُ أَن يُوقِعَ بَيْنَكُمُ ٱلْعَدَٰوَةَ وَٱلْبَغْضَآءَ فِى ٱلْخَمْرِ وَٱلْمَيْسِرِ وَيَصُدَّكُمْ عَن ذِكْرِ ٱللَّهِ وَعَنِ ٱلصَّلَوٰةِ ۖ فَهَلْ أَنتُم مُّنتَهُونَ ሰይጣን የሚፈልገው በሚያሰክር መጠጥና በቁማር በመካከላችሁ ጠብንና ጥላቻን ሊጥል አላህን ከማውሳትና ከስግደትም ሊያግዳችሁ ብቻ ነው፡፡ ታዲያ እናንተ (ከእነዚህ) ተከልካዮች ናችሁን (ተከልከሉ)፡፡>

2፥268<ሰይጣን እንጻትለግሱ ድኽነትን ያስፈራራቺኋል። በመጥፎም ያዛቺኋል።> 35፥6<ሰይጣን ለእናንተ ጠላት ነው>

ከላይ ለናሙና እንዳየናቸው ሰይጣን በብዙ ቦታወች ላይ ሲጠቀስ የተጠቀሰው ግን ከነ ባህሪያቱ ነው ማለትም አሳሳችነቱ ጋር አብሮ ልክ እንደዚህም ኢሳ [አለይሂ ሰላም] ከነ ነብይነቱ ነው በብዙ ቦታወች ላይ የተጠቀሰው ። እንደናንተ በቁጥር ብዛት እምንሄድ ቢሆን ሰይጣን ከ ኢሳ ይበልጣል ማለት ነው ስለ ዚህ የቁጥር መብዛት ለክብር እና ለልቅና ምንም ፋይዳ የለውም ሲቀጥል ደግሞ ቁርአን ለሙሃመድ[ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለም] ነው የወረደው ታዲያ ለሙሃመድም[ሰለሏሁ አለይሂ ወሰለምም] የወረደው ስለ አለፉት ነብያቶች ይተርክለታል

20፥99< كَذَٰلِكَ نَقُصُّ عَلَيْكَ مِنْ أَنۢبَآءِ مَا قَدْ سَبَقَ ۚ وَقَدْ ءَاتَيْنَٰكَ مِن لَّدُنَّا ذِكْرًۭا እንደዚሁ በእርግጥ ካለፉት ወሬዎች ባንተ ላይ እንተርካለን፡፡ ከእኛም ዘንድ ቁረኣንን በእርግጥ ሰጠንህ፡፡> በዚህም ምክኒያት ነው የ ኢሳ [አለይሂ ሰላም] ታሪክ የተተረከለት ለዛም ነው ስሙ በብዛት የተጠቀሰው

ሌላ ደግሞ ከዚህ የበለጠ እሚያስቀኝ ጥያቂያቸው <የነብዩ ሙሃመድ እናት ስም ቁርአን ላይ አልተረቀሰም> መጀምሪያ አላህ ሱብሃነሁ ወተአላ ለኛ እሚጠቅመንን ሁሉ ተርኮልናል

11፥120< وَكُلًّۭا نَّقُصُّ عَلَيْكَ مِنْ أَنۢبَآءِ ٱلرُّسُلِ مَا نُثَبِّتُ بِهِۦ فُؤَادَكَ ۚ وَجَآءَكَ فِى هَٰذِهِ ٱلْحَقُّ وَمَوْعِظَةٌۭ وَذِكْرَىٰ لِلْمُؤْمِنِينَ ከመልክተኞቹም ዜናዎች (ተፈላጊውን) ሁሉንም ልብህን በርሱ የምናረካበትን እንተርክልሃለን፡፡ በዚህችም (ሱራ) እውነቱ ነገር ለምእምናን ግሳጼና ማስታወሻ መጥቶልሃል፡፡>

ታድያ የነብዩን እናት ማወቃቺን ብናውቅ ጥሩ ነው ግን ለኛ በጣም አስፈላጊ [አንገብጋቢ] አደለም ያም ቢሆን በሃዲስ ተነግሮናል፡፡ እሚገርማቺሁ ይህ ጥያቂያቸው አንድ ነገር ያስታውሰኛል እውነት ቁርአን የሙሃመድ ድርሰት ቢሆን ኑሮ ለምን የእናቱን ስም በሱ ላይ አያወሳበትም ነበር ይህ ሙሉ በሙሉ የአላህ ቃል ለመሆኑ እንኳ ትልቅ ማስረጃ ነው እሚሆነው አያቺሁ አንድ በራሱ ድርሰት ላይ የእናቱን የአባቱን የዘሩን ምናምን ስም ይጨምር ነበር ግን ይህ የሰው ድርሰት ሳይሆን የአላህ ሱብሃነሁ ወተአላ ቃል ስለሆነ ነው

ወሰላሙአለይኩም