ሰኸምሬ ሳንኽታዊ 3 ነፈርሆተፕላይኛ ግብጽ2ኛው ጨለማ ዘመን (16ኛው ሥርወ መንግሥት) ምናልባት 1637-1636 ዓክልበ. አካባቢ የገዛ ፈርዖን ነበረ።

ሰኸምሬ ሳንኽታዊ 3 ነፈርሆተፕ
ነፈርሆተፕ (ቀኝ) በተጎዳ ጽላት ላይ
ነፈርሆተፕ (ቀኝ) በተጎዳ ጽላት ላይ
የግብጽ ፈርዖን
ግዛት 1637-36 ዓክልበ. ግ.
ቀዳሚ 8 ሶበክሆተፕ
ተከታይ መንቱሆተፒ
ሥርወ-መንግሥት 16ኛው ሥርወ መንግሥት

ስሙ «ሰኸምሬ ሳንኽታዊ ነፈርሆተፕ» የሚታወቀው ከአንድ ቅርስ ብቻ ነው። ይህ ጽላት በጣም የተጎዳ ቢሆንም «የጤቤስ ንጉሥ» እንደ ነበር ይገልጻል። ብስሙ ውስጥ «ታዊ» ቢገኝም፣ ይህ በሂክሶስ ዘመን ስለ ነበር፣ እንዲሁም አቢዶስአቢዶስ ሥርወ መንግሥት ነጻ እንደ ሆነ ስለሚታሰብ፣ 3 ነፈርሆተፕ በእውነት በታችኛ ግብጽ ላይ እንደ ገዛ አይታሰብም።

ከዚህ በቀር በቶሪኖ ቀኖና ላይ በአንድ ክፍል «ሰኸምሬ ፫ አመት፣ ሰኸምሬ ፲፮ አመት፣ ሰኸምሬ... ፩ አመት» ሲል ይህ ክፍል ባብዛኛው የ16ኛው ሥርወ መንግሥት እንደ ሆነ ይታመናል። ሦስተኛው የተዘረዘረው ለ፩ አመት የገዛው ሰኸምሬ 3 ነፈርሆተፕ እንደ ነበር ይገመታል።

ቀዳሚው
8 ሶበክሆተፕ
ግብፅ (ጤቤስ) ፈርዖን
1637-1636 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
መንቱሆተፒ