ጉኑኖ
ጉኑኖ በኢትዮጵያ ወላይታ ውስጥ ያለ ከተማ ነው። ከተማው በወላይታ ዞን የዳሞት ሶሬ ወረዳ የአስተዳደር ዋና ከተማ ሆኖ ያገለግላል። ጉኑኖ የኢትዮጵያ ርዕሰ መዲና ከሆነችው ከአዲስ አበባ በ345 ኪሎ ሜትር እና ከወላይታ ዞን ዋና ከተማ ሶዶ 17 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ይገኛል። በጉኑኖ አቅራቢያ የሚገኙት ሌሎች ወረዳዎች; በደቡብ በሶዶ ዙሪያ፣ በሰሜን ምዕራብ በቦሎሶ ቦምቤ፣ በምዕራብ በኪንዶ ኮይሻ፣ እና በምስራቅ በቦሎሶ ሶሬ። የጉኑኖ ከተማ በካርታ ላይ የሚገኘው 6°55'21"ሰሜን 37°38'57"ምስራቅ ነው።
ጉኑኖ Gununo Ambbaa | |
ከተማ | |
![]() | |
አገር | ![]() |
ክልል | ደቡብ ብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል |
ዞን | ወላይታ |
ወረዳ | ዳሞት ሶሬ |
ካንቲባ | ወንድሙ ደረጀ |
የህዝብ ቁጥር
ለማስተካከልበ2020 ኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ባደረገው ትምቢያ መሰረት የጉኑኖ አጠቃላይ ህዝብ ብዛት 15,700 ነው። ከዚህ ውስጥ 7,963 ወንዶች ሲሆኑ 7,737 ደሞ ሴቶች ናቸው።[1] በዚህ ከተማ ውስጥ ያሉ የሴቶች የመራቢያ ዕድሜ ቡድን ወደ 23.3% ወይም በቁጥር 6,360 ገደማ ነው። በከተማው ውስጥ አንድ ጤና ጣቢያ እና ሶስት የግል ክሊኒኮች ብቻ አሉ።
ምንጮች
ለማስተካከል- ^ "የጉኑኖ ከተማ ህዝብ ቁጥር". Archived from the original on 2022-07-07. በ2022-02-04 የተወሰደ.