የጓደኛህን ቀን ይስጥህ

(45)አለቃ ገብረ ሀና ከሸዋ ወደ ጎንደር ግብዣ ተጠርተው ግብዣው ላይ ለመገኘት ይጓዙና ጎጃም ላይ ሲመሽባቸው ወደ አንድ ኮማሪት ቤት ይገቡና መጠጥ አዘው ቁጭ ይላሉ። አለቃ ደርባባዋ ኮማሪትዋ ቃ ትላቸውና እዛ ለማደር ያስባሉ። በጣም ሲመሽም ኮማሪትዋ ሌሎቹን ሰዎች ታስወጣና አለቃን አይታ እኚሕ ሽማግሌስ ምንም አያደርጉኝም ብላ ለሳቸው መደብ ላይ አንጥፋ ከጎናቸው ፈንጠር ብላ ትተኛለች። በነገራችን ላይ ሴትየዋ አንድ እግሯ የተቆረጠ እና በአርተፊሻል እግር ነበር የምትራመደው። አለቃም ለሊት ላይ ወደ ሴትየዋ ተጠግተው አሰስ ዳሰስ ማድረግ ሲጀምሩ ሴትየዋም ነቅታ በደህና እግሯ በርግጫ ብላ ትመታቸዋለች። አለቃም ቀበል ያደርጉና «የጓደኛህን ቀን ይስጥህ ሌላ ምን እላለሁ» ብለው እርፍ።