የመርዌ ጽሕፈት ከ200 ዓክልበ. ያሕል ጀምሮ በመርዌ መንግሥት (ዛሬ ሱዳን) የመርዌ ቋንቋ የተጻፈበት ፊደል ነበር። የወጣው ከግብፃዊሃይሮግሊፊክዴሞቲክ ጽሕፈቶች ነበር። ከመርዌ መንግሥት በኋላ በተከተሉት በኖባ መንግሥታት ደግሞ ክርስትና እስከ ገባ ድረስ ምናልባት ይጠቅም ነበር፡፡ ከክርስትና በኋላ የጥንታዊ ኖባ ቋንቋ የተጻፈበት በግሪክ ፊደል ሲሆን ከዱሮ መርዌ ጽሕፈት 3 ምልክቶች ተጨምረው ነበር፡፡

(*- የ"ተ" እና የ"ቶ" ስዕሎች በስህተት እዚህ ተገልብጠዋል፡፡)

በጠቅላላ 23 ምልክቶች ነበሩበት፡፡ ከነዚህ መሀል 4 አናባቢዎች፣ እነሱም /አ/, /እ/, /ኢ/, ና /ኦ/ ነበሩ፡፡ የተናባቢ ምልክቶች ለብቻ ሲታዩ የ/አ/ ድምጽ ያሰሙ ነበር፡፡

ለዚህ ፊደል ሁለት አይነቶች እነሱም ሃይሮግሊፊክና ዴሞቲክ ነበሩ፡፡ የሃይሮግሊፊክ ቅርጾች በተለይ የሚገኙ በሐውልቶች ነው፡፡ እሱ ከላይ እስከ ታች ይጻፍ ነበር፣ ዴሞቲክ ከቀኝ እስከ ግራ ይጻፍ ነበር፡፡ ሁለት ወይም ሦስት ነጥብ ቃላት ለመለየት ጠቀመ፡፡

የፊደሎቹ ፍች የገለጸው ሊቅ እንግሊዛዊፍራንሲስ ልወልን ግሪፊስ1901 ዓ.ም. ነበር፡፡ ዳሩ ግን እስከ ዛሬ ድረስ ቋንቋው እራሱ በደንብ አይታውቅም፡፡

አፍአዊ ድረ ገጾች ለማስተካከል