ዛንዚባርስዋሂሊ /ዛንዚባር/; አረብኛ /ዚንጂባር/ የታንዛኒያ የራስ ገዥ ደሴት ክልል ነው። ከዋናው የባህር ዳርቻ 25-50 ኪ.ሜ (ከ 16 - 31 ማይሜ) በሆነችው ሕንድ ውቅያኖስ ውስጥ ከሚገኘው የዛንዚባር አርኪፔላጎ የተዋቀረ ሲሆን ብዙ ትናንሽ ደሴቶችን እና ሁለት ትልልቆችን ያቀፈ ነው። ኡንጉጃ (ዋናው ደሴት፣ በተራው አጠቃቅም «ዛንዚባር» ይባላል) እና ፔምባ ደሴት የተባለው ትልልቆቹ ናቸው። ዋና ከተማው በኡንጉጃ ደሴት ላይ የምትገኘው ዛንዚባር ከተማ ናት። ታሪካዊ ቦታዋ ስቶን ታውን ሲሆን ይህም የዓለም ቅርስ ናት ።

የዛንዚባር ዋና ዋና ኢንዱስትሪዎች ቅመማ ቅመም ፣ ራፊያ ዘምባባ፣ እና ቱሪዝም ናቸው። በተለይም ደሴቶቹ ቅርንፉድገውዝቀረፋ እና ጥቁር በርበሬ ያመርታሉ ። በዚህ ምክንያት የዛንዚባር አርኪፔላጎ ፣ ከታንዛኒያ ማፊያ ደሴት ጋር አንዳንድ ጊዜ በአካባቢው “የቅመም ደሴቶች” ተብለው ይጠራሉ (ከኢንዶኔዥያው ከማሉኩ ደሴቶች የተወሰደ ቃል ነው) ።

ዛንዚባር የዛንዚባር ቀይ ጉሬዛየዛንዚባር አነር መሳይ መጠማት እና የጠፋ ወይም ብርቅዬ የዛንዚባር ነብር መኖሪያ ነው።