ስለ አዘዞ ከተማ የሚያመለክት ትንሽ ሃተታ

አዘዞ የተባለችው ከተማ በሽማግሌዎችና ሊቃውንት አንደበት ሲነገር የነበረው አፈ ታሪክ የስሟ ትርጓሜ አንዲህ ነው፡፡ ይህች አዘዞ የተባለች ከተማ የጎንደር ነገስታት በሞቱ ጊዜ ይቀበሩባት ነበር፡፡ የን ግዜም ሲሞቱ የትዕዛዛቸውና የኑዛዜአቸው ቃል ከመቃብረ መንግስት መዝገብ ውስጥ እንዲገኝ እያሉ ከሞቱ በኋላ የሚሆነውን የኑዛዜአቸውንና የትዕዛዛቸውን ቃል ስለሚያስቀምጡበት ያዘዙበት ወይም የተናዘዙበት ቦታ በማለት ፈንታ ከዘመን ብዛት አዘዞ ተባለች እንጂ ጥን ስሟ አዝዞ ወይም ተናዝዞ ሞተ ማለት ነው፡፡

ምንጭ፡ አባ ጋስፖሪኒ ጉማ፤ የኢትዮጵያ ታሪክ፤ ከረጅሙ ባጭሩ የተውጣጣ፡፡