ባላምበራስ ሞገስ እርጥቦ

ባላምበራስ ሞገስ እርጥቦ በጎጃም ክፍለ ሀገር በቆላ ደጋ ዳሞት አውራጃ በሽኩዳድ ወረዳ ተወለዱ። ለአቅመ አዳም ሲደርሱ ባለቤታቸውን ወይዘሮ ፍልፍሏ ታዬን (የፊታውራሪ ታዬ ልጅ) አግብተው ሶስት ልጆችን ወልደዋል። ደስታ ሞገስ፣ ታደሰ ሞገስ እና ተፈራ ሞገስ። ባላምበራስ ሞገስ የአፄ ምኒልክ አንጋች ሆነው በማገልገል ላይ እያሉ ለከፋ ጠቅላይ ግዛት አስተዳዳሪ ሆነው በአፄ ምኒልክ ተሾመው አገልግለዋል።