ታክሲላ በአሁኑ ፓኪስታን የነበረ የጥንት ከተማ ነው።

ታክሲላ
ተክሸሺላ፣ ተከሺላ
ታላቅ ቁልል
ሥፍራ
ታክሲላ is located in ፓኪስታን
{{{alt}}}
መንግሥት ገንዳረ፣ ፋርስ፣ ሕንድ፣ ባክትርያ፣ ኩሻን መንግሥት፣ ጉፕታ መንግሥት
ዘመን 1000 ዓክልበ. - 460 አም
ዘመናዊ አገር ፓኪስታን
ጥንታዊ አገር ገንዳረ

ስሙ በሳንስክሪት ተክርሸ-ሺላ «የተቆረጠ ድንጋይ» ነበረ፣ በፓሊኛ ተከሺላ ሆነ። ይህም በኋላ በግሪክኛ «ታክሲላ» ሆነ።

ከተማው በ1000 ዓክልበ. ያህል እንደ ተመሠረተ ይታስባል። የንግድ ማዕከልና የገንዳረ መንግሥት ዋና ከተማ ሆነ። ከተማው በሂንዱኢዝምቡዲስምጃይኒስም አፈ ታሪክ ይገኛል።

የትምህርት ቤት ተቋም ለማስተካከል

የታክሲላ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ልክ መቼ እንደ ተመሠረተ አይታውቅም፣ ግን ከጎታማ ቡዳ ዘመን (500 አክልበ. ግድም) በኋላ የቡዲስም ትምህርት ተቋም እንደ ሆነ ይመስላል። ይህም ተቋም ስንኳ ከፕላቶ አካዳሚ በፊት በመሆኑ ምናልባት የዓለሙ መጀመርያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ሊባል ይችላል።

በተቋሙ ውስጥ ከተማሩት ጥናቶች መካከል፦ ቬዳዎቹ፣ ቀስትን ማስፈንጠር፣ የጦር ሠልፍ፣ ማደን፣ የዝሆን ወግ፣ ሕግሕክምና ነበሩ። ተማሪ በአስራ ስድስት አመት እድሜ ይጀመር ነበር፣ ከመላው ሕንድ አገር ተጓዝተው ይደርሱ ነበር። ለተማሮች ገንዘብን አላስከፈሉም፣ ድሆች የሆኑትም በምሽቱ፣ ባለሀብቶችም በቀን ይማሩ ነበር። ትምህርቱ አስተማሪው እስከሚጨርስ ድረስ ቀጠለ፣ እንጂ እንደ ዘመናዊ ዩኒቨርስቲ ስርዓት ፋከልቲ አዳራሽ ወይም ዶርሚቶሪዎች ወይም የተወሰነ ጊዜ ወይም ዲግሪ አልነበረም። የማንም መንግሥት አስተዳደር አልነበረውም፤ ከሀብታም ዜጎች ግን የልግሥና ድጋፍ ይቀበሉ ነበር።

በታክሲላ ተቋም ታዋቂ ከሆኑት ተማሮች መካከል፦

ታሪክ ለማስተካከል

ከተማው በፋርስ ንጉሥ ፩ ዳርዮስ በ524 ዓክልበ. ተያዘ፣ የፋርስም ነገሥታት ለመቶ ዓመት ያህል ይገዙት ነበር።

በ334 ዓክልበ. ታላቁ እስክንድር ከተማውን ከንጉሡ አምቢ ያዘ። ግሪኮች ከተማው ሀብታምና በጥሩ አስተዳደር እንዳገኙት ጻፉ።

ከዚህ ትንሽ በኋላ የማውርያ መንግሥት (ሕንድ) ንጉሥ ቻንድራጉፕታ ያዘው። አማካሪው ቻነክየ ወይም ካውጢልያ ዝነኛ መጽሐፉን አርጠሻስትረ («የምጣኔ ሀብት ዕውቀት») የጻፈው በታክሲላ እንደ ነበር ይባላል። የቻንዳራጉፕታ ልጅ አሾካ በተለይ ቦታውን የቡዲስም ጥናት ማዕከል አደረገው።

 
የታክሲላ መሐለቅ 170 ዓክልበ. ግድም

በ180 ዓክልበ. የግሪኮች ባክትርያ መንግሥት ታክሲላን ያዙ። ከዚያም በ98 ዓክልበ ሳካዎች ያዙት። የገንዘብ (መሐለቅ) መሥሪያ ቤት በታክሲላ ነበራቸው።

በ28 ዓክልበ. ግድም የጳርቴ ሰዎች ወርረው ያዙት። የኢየሱስ ሐዋርያ የሆነው ቅዱስ ቶማስ38 ዓም ወደ ታክሲላ እንደ ደረሰ ይታመናል። ከዚያ በኋላ ወደ ሕንድ ሄዶ ወንጌልን እዚያም ሰበከ። የግሪክ ፈላስፋ አፖሎንዮስ ዘቱዋና ደግሞ በዚያው ወቅት ታክሲላን እንደ ጎበኘ ይባላል።

ከ68 ዓም በፊት ታክሲላ በኩሻን መንግሥት ተያዘ። ከ370 ዓም በኋላ የጉፕታ መንግሥት (ሕንድ) ያዘው። በዚህ ዘመን የሐርሰንደልፈረስጥጥብርሉል (ዕንቁ)ቅመም ንግድ ማዕከል ነበረ። የቻይና ተጓዥ ፋሥየን ታክሲላን በ400 ዓም ግድም ጎበኘ።

በ440 ዓም ኪዳራውያን (የሁኖች ወገን) ወርረው ጥቃት በታክሲላ ላይ ጣሉ። ከዚያ በኋላ በዙሪያው ጦርነት ይበዛ ነበር። በመጨረሻ በ460 ዓም ግድም ሄፕታላውያን ወይም «ነጭ ሁኖች» ቦታውን ትምህርት ቤቱንም አጠፉ።

የቻይና ተጓዥ ሥወንዛንግ ዙሪያውን በ630 ዓም በጎበኘው ጊዜ ከጥቂት መኖክሶች በቀር ፍርስራሽ ብቻ አገኘ።

ፍርስራሹ እንደገና በ1855 ዓም በሥነ ቅርስ ሊቆች ተገኘ።