ሰዴ ወረዳ በ ምስራቅ ጎጃም ዞን የሚገኝ ወረዳ ነው። በ2009 አ.ም 16 የደጋ ቀበሌዎችን በመያዝ ከ ሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ተቀንሶ የተመሰረተ ወረዳ ነው። የወረዳው ከተማ ሰዴ ይባላል። ሰዴ ከተማ ከ ሞጣ ያለው የመስመር ርቀት በ ቀራንዮ መስመር 32 ኪሎሜትር በ ቻክ መድኃኔዓለም በድሮው የእግር መንገድ 16 ኪሎሜትር ነው። ከተማው በቀደሙት ሰዎች ሰዴ ጊዎርጊስ እየተባለ ይጠራል። ይህ አጠራር በከተማው ከሚገኘው ጥንታዊ ሰማዕቱ ቅዱስ ጊዎርጊስ ቤተክርስቲያን ጋር የተያያዘ ነው። ሰዴ እሰከ 1974 በ ሞጣ አውራጃ ስር የ ሁለት እጁ እነሴ ወረዳ አስተዳደር መቀመጫ ነበረች። የ ሰዴ ወረዳ በሰሜን የ ሁለት እጁ በምዕራብ ቢቡኝ በደቡብ ደባይ ጥላትግን በምስራቅ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ያዋስኑታል ። በወረዳው ሁለት ባንክ ማለትም መንግስታዊው የ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እና የግል ባንክ የሆነው አቢሲኒያ ባንክ2011 አ.ም ጀምሮ አገልግሎት እየሰጡ ነው። በወረዳው ሶስት ጤና ጣቢያዎች ሰዴ ፣ ከርነዋሪ እና ጎይባ አግልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ።

ሰዴ ከተማ 1992 ዓ.ም የ ውሃ በ 2000 ዓ.ም ደግሞ የመብራት ተጠቃሚ ሆናለች ።

አየር ንብረት ለማስተካከል

የ ሰዴ ከተማ ከባህር ወለል በላይ 2550 ሜትር ከፍታ ላይ ትገኛለች። ከተማዋን ሰዴን ጨምሮ አብዛኛው ቀበሌዎች ደጋማ አየር ንብረት አላቸው። የ ሰዴ ከተማኬክሮስ እና ኬንትሮስ ( ላቲቲዪድ እና ሎንግቲዪድ መገኛው በ10°55′ ሰሜን ኬክሮስ እና 37°53′ ምሥራቅ ኬንትሮስ ላይ ነው።


ሕዝብ ብዛት ለማስተካከል

በ 2011 አም በነበረው መረጃ የወረዳው ህዝብ ብዛት 101763 ነበር። በ1999 አም ማዕከላዊ ስታስቲክስ ኤጀንሲ ባደረገው የ ሕዝብና ቤቶች ቆጠራ በ ሰዴ ከተማ 2309 ( ሁለት ሺ ሶስት መቶ ዘጠኝ ) ጠቅላላ ሕዝብ ነበረ። ከነኚም መካከል 1296 ወንድ ሲሆኑ ቀሪዎቹ ደግሞ ሴቶች ነበሩ። ከ 1999 አም በፊት 1987 አም በተደረገው አገር አቀፍ ሕዝብና ቤቶች ቆጠራ በ 408 አባዎራዎች ቤት የ ሰዴ ጠቅላላ ሕዝብ 1345 ነበረ። ከእነዚህ 533 ወንድ ሲሆኑ 812 ደግሞ ሴቶች ነበሩ። በዚህ ቆጠራ መሰረት አብዛኛው የ ከተማዋ ሕዝብ 94.6 % ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሀይማኖት ተከታይ ሲሆን 5.4% ደግሞ ሙስሊም ነበሩ። ሰዴ የ 24 ሰዐት የመብራት አገልግሎት ተጠቃሚ ከሆነች ጀምሮ የ የከተማዋ ህዝብ ብዛት ጨምሯል ። በተለይ ከተማዋ ራሷን ችላ የወረዳ ማዕከል ከሆነች ጀምሮ የከተማዋ ህዝብ ብዛት በአያሌ ጨምሯል።

ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ የሰዴ ወረዳ አስተዳዳሪዎች በቅደም ተከተል ለማስተካከል

  1. አቶ አብርሀም አያሌው
  2. አቶ መላኩ ከበደ
  3. ደመቀ ንጉሴ

ስዩም ይዘንጋው ድንቁ (talk) 20:29, 8 ዲሴምበር 2020 (UTC)