1 ፑዙር-አሹር (ወይም ፑዙር-አሺር) የአሹር ገዥ ወይም ንጉሥ ነበር። የአሦር ነገሥታት ዝርዝር ቢጠቅሰውም ሕልውናው ከሥነ ቅርስ ገና አልተረጋገጠም። ምናልባት 1914-1907 ዓክልበ. አካባቢ ገዛ።

ስሙ ሴማዊ ስለሆነ («የአሹር አገልጋይ»)፣ በአሦር ነገሥታት ዝርዝርም ላይ ከእርሱ የቀደሙት ስሞች ሴማዊ ስለማይመስሉ፤ በዚህ ወቅት አዲስ ሴማዊ (አሞራውያን ወይም አካድ) ሥርወ መንግሥት በአሦር እንደ መሠረተ ይገመታል። ነገር ግን በዝርዝሩ ያልተገኘ ሰው ዛሪቁምኡር ንጉሥ አማር-ሲን ዘመን የአሹር ገዥ እንደ ነበር ከቅርስ ስለሚታወቅ፤ እሱ የፑዙር-አሹር ቀዳሚ ይሆናል። ዛሪቁምም ሴማዊ ስም ነው።

ከነገሥታት ዝርዝሩ ውጭ፣ በኋላ የነገሡት የአሦር ነገሥታት አንዳንዴ በጽሑፋቸው ይጠቅሱት ነበር። አሹር-ረዕም-ኒሸሹ (1409-1402 ዓክልበ.)ና 3 ስልማናሶር (866-831 ዓክልበ.) እንደ መዘገቡት፣ይህ ፑዙር-አዙር ቀድሞ ኪኪያ የሠራውን የከተማው ግድግዳ ካሳደሱት ነገሥታት መካከል ነበረ።

ቀዳሚው
ዛሪቁም
አሹር ገዥ
1914-1907? ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ሻሊም-አሁም