ፋሺዝም የፖለቲካዊ ርዕዮት ዓለም ሆኖ ሥልጣናዊነትን እና ጽንፈኛ ብሔርተኝነትን አዋህዶ የያዘ ነው። ከፋሽዝም መገለጫዎች ውስጥ፣ ፈላጭ ቆራጭነት፣ ተቃራኒ ሐሳቦችንም ሆነ ማሕበረሰቦች በፍጹም ማፈን፣ ኢኮኖሚውንና ማህበረሰቡን ደግሞ ዝንፍ በማይል ሥነ-ሥርዓት ማስተዳደር ይጠቀሳሉ። የፋሽዝም ኣባት እና ደራሲ የጣሊያኑ መሪ ቤኔቶ ሞሶሊኒ ነው።