ጉዕል (ኮሪይኛ፦ 구을) በኮርያ ልማዳዊ አፈ ታሪክ በጥንታዊ ኮርያ (ጎጆሰን) የነገሠ ንጉሥ ወይም «ዳንጉን» ነበር። እርሱ ከዳንጉን ኦሳጉ መንግሥት ቀጥሎ ገዛ። ጉዕል ከኦሳጉ ፭ ሚኒስትሮች «ያንጋ» የተባለው ነበር።

በጠቅላላ ለ፲፮ ዓመታት(ምናልባት 1881-1865 ዓክልበ.) እንደ ነገሠ ይጻፋል። ከዚያ በኋላ ታልሙን ተከተለው።

ኋንዳን ጎጊ ለማስተካከል

1903 ዓም. በኮሪይኛ የተዘጋጀው ዜና መዋዕል ኋንዳን ጎጊ ስለዚሁ አፈታሪካዊ ዘመን መረጃ ይሰጣል፤ ሆኖም በብዙ የኮርያ መምህሮች ዘንድ ይህ መጽሐፍ እንደ ትክክለኛ ታሪክ አይሆንም። ጉዕል ካደረጋቸው ሥራዎች መካከል ዋና ዋናዎቹ እንዲህ ናቸው፦

  • በ1879 ዓክልበ. ግድም በግንቦት የአንበጣ ደመና ሜዳዎቹን ሁሉ ሞላ። በዳንጉን ጸሎት ግን ከጥቂት ቀን በኋላ ተበተኑ።
  • በ1873 ዓክልበ. ግድም የ«ሺንዶክ» (?) አገር ሰዎች በድንገት በወደብ ከባሕር ደረሱ።
  • በ1865 ዓክልበ. ግድም ዳንጉን ጉዕል ዓረፈ፤ ሚኒስትሩም ታልሙን ተከተለው
ቀዳሚው
ኦሳጉ
ጆሰን ዳንጉን
1881-1865 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ታልሙን

ዋቢ ምንጭ ለማስተካከል