ጅጅጋ በምስራቅ ኢትዮጵያ የሚገኝ ከተማ ነው። ከተማው ከሐረር 80 ኪ.ሜ. ይርቃል። በቀድሞው ሐረርጌ ክፍለ-ሀገር የሚገኝ ከተማ ሲሆን አሁን የሶማሌ ክልል ዋና ከተማ ነው። በ1994 እ.ኤ.አ. ከተማው 56,821 ሰዎች ነበሩት። በ1998 ማዕከላዊ የስታትስቲችስ ባለስልጣን እንደተመነው ጅጅጋ የ98,076 ሰው መኖሪያ ስትሆን ከነሱም 50,355 ወንዶችና 47,721 ሴቶች ይገኙበታል። ከተማው በ9°10' ሰሜን ኬክሮስ እና 42°48' ምስራቅ ኬክሮስ ይገኛል።


[[