አጼ ጅን አሰገድ የአጼ ይግባ ጽዮን ልጅ የአጼይኩኖ አምላክ የልጅ ልጅ ሲሆኑ ከ1297-1298 ለአንድ አመት የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ነበሩ። ታሪክ ጻህፍት እንደሚሉት አባታቸው ይግባ ጽዮን 5 ወንድ ልጆች ስለነበሩዋቸውና የትኛው ንጉስ እንዲሆን መምረጥ ስላልቻሉ እያንዳንዱ ወንድ ልጅ አንድ አንድ አመት እንዲነግስ ቃል ስላስገቡዋቸው 1 አመት ብቻ ነግሰዋል[1] [2]

ዋሊስ በድጅ የተሰኘው የታሪክ ተመራማሪ ተፎካካሪ የንጉሳዊ ቤተሰቦችን አምባ ግሸን ማሰር የጀመሩት እኒሁ ንጉስ ናቸው ይላል። ይህንም ያደረጉት አስቸጋሪ ወንድማቸውን ሳባ ሰገድን ከራሳቸው ለማራቅ ነበር ይላል ዋሊስ። ከሳባ ሰገድ በተጨማሪ ሶስቱ ወንድሞቻቸውንና የራሳቸውን ልጅ አምባው ላይ እንዳሰሩ ዋሊስ ያትታል።[3]

ሆነም ቀረም ጅን አሰገድ የነገሱት ለአንድ አመት ብቻ ነበር።


ማጣቀሻወች ለማስተካከል

  1. ^ Paul B. Henze, Layers of Time, A History of Ethiopia (New York: Palgrave, 2000), p. 60.
  2. ^ ታደሰ ታምራት, Church and State in Ethiopia (Oxford: Clarendon Press, 1972), p. 72.
  3. ^ E. A. Walis Budge, A History of Ethiopia: Nubia and Abyssinia, 1928 (Oosterhout, the Netherlands: Anthropological Publications, 1970), p. 287. According to G.W.B Huntingford, this information comes from the Jesuit historian Pedro Páez, who was told this story by Emperor Susenyos (The Historical Geography of Ethiopia [London: The British Academy, 1989], p. 75).