ድንጋይ ዘመን በ«ሦስቱ ዘመናት» አስተሳሰብ ከናስ ዘመን አስቀድሞ የነበረው ዘመን ነው። በአጠቃላይ እንደ ተለመደ ከ3125 ዓክልበ. ያህል በፊት ያመልክታል። በዚህ ዘመን አብዛኞቹ መሣርያዎችና እቃዎች የተሠሩ ከድንጋይ ነበር።

ናስ ጥቅም በጥንታዊ ግብጽ ከ3125 ዓክልበ. ግድም ጀምሮ ይታወቅ ነበር። ይህም ደግሞ በአለም ላይ የጽሑፍ መጀመርያ ወቅት ስለነበር፣ የታሪክ መጀመርያ ደግሞ ይባላል። እንግዲህ የ«ድንጋይ ዘመን» እና የ«ቅድመ-ታሪክ» ትርጉም አንድላይ ሊሆን ይችላል።

የዚህ አከፋፈል ዋጋ አጠያያቂ ነው። በብዙ ቦታዎች የናስና የብረት ዕውቀት የገቡት በአንድ ጊዜ ነበረ። ለምሳሌ በስሜን አሜሪካ በኩል፣ አውሮፓውያን 1500 ዓም ያህል ሳይገቡ ኗሪዎቹ የብረታብረት ቀለጣ እንደነበራቸው አይታስብም፤ ከተደቀደቀ መዳብወርቅብር በቀር ብዙ የብረታብረት እቃዎች አላወቁም ነበር። የመዳብና የነሐስ ቀለጣ ግን በደቡብ አሜሪካ ይታወቅ ነበር፣ ከ800 ዓም ግድም ጀምሮ በመካከለኛ አሜሪካ ደግሞ ይታወቅ ነበር።