የብሪታንያ መንግሥት (British Empire) ኢንግላንድስኮትላንድ1699 ዓም እንደ ታላቅ ብሪታንያ ከተዋሐዱ ጀምሮ ከሌሎች ባህር ማዶ ጥገኛ ግዛቶች ጭምር ማለት ነው።

የብሪታንያ መንግሥት በጫፉ፣ 1912 ዓም

ከ1699 ዓም አስቀድሞ የኢንግላንድ መንግሥት በአሜሪካአትላንቲክ ውቅያኖስ አጠገብ፣ እንዲሁም በካሪቢያን ባህር ዙሪያ አንዳንድ ቅኝ አገራት መሠርተው ነበር። በ1775 ዓም ከአሜሪካዊ አብዮት ቀጥሎ 13ቱ ቅኝ አገሮች ተነቅለው የራሳቸው አገር (ዩናይትድ ስቴትስ) ሆኑ። ካናዳ ግን ለዩናይትድ ኪንግደም ግዛት ሆና ቀረች።

የብሪታንያ ፪ኛ መንግሥት የተባለው ከዚህ በኋላ በተለይ በእስያ፣ በአፍሪካና በአውስትራሊያ ይስፋፋ ጀመር። የግዛቱም ጫፍ በ1912 ዓም ያህል ተከሰተ። ከ2ኛ ዓለማዊ ጦርነት ቀጥሎ ብዙዎቹ ቅኝ አገሮቿ ነጻነታቸውን በሰላማዊነት አገኙ። በአሁኑ ሰዓት ለዩናይትድ ኪንግደም 14 ጥቃቅን ባህር ማዶ ግዛቶች ብቻ ቀርተዋል። በተጨማሪ የዩናይትድ ኪንግደም ንግሥት ዳግማዊት ኤልሳቤጥ እስካሁን የሌሎች 15 አገራት ንግሥት ሆነው ቀርተዋል።