የ ዩ ዪ ያ ዬ ይ ዮ



አቡጊዳ ታሪክ

የመን (ወይም የማን) በጥንታዊ አቡጊዳ ተራ ዐሥረኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓንአራማያዕብራይስጥሶርያም ፊደሎች ዐሥረኛው ፊደል «ዮድ» ይባላል።

ዓረብኛ ደግሞ ተመሳሳይ ፊደል «ያእ» ተብሎ በ«አብጃድ» ተራ 10ኛ ነው። (በዘመናዊ ተራ ግን 28ኛው ነው።)

ታሪክ ለማስተካከል

ተመሳሳይ ግብፃዊ ስዕል («ዐ») ቅድመ-ሴማዊ ሣባ ግዕዝ
D36
   


የየመን መነሻ ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት እንደ ሆነ ይታስባል። በዚህ ጽሕፈት ፊደሉ የእጅ ስዕል መስለ። ለዚህም ተመሳሳይ የግብጽ ሀይሮግሊፍ ነበር። አጠራሩ ግን «ዐ» ነበር። በግብፅ የሠሩት ሴማውያን ግን በቋንቋቸው «ዮድ» ስላሉት፣ ይህ ስዕል «ይ» ሆኖ እንዲሰማ መጣ። በግዕዝ ቃሉ «እድ» ሆኖ በዚሁ ድምጽ ስለማይጀመር፣ በ«ዮድ» ፈንታ የፊደል ስም «የመን» (ማለት ቀኝ እጅ) ይባላል።

ከነዓን አራማያ ዕብራይስጥ ሶርያ ዓረብኛ
    י  


የከነዓን «ዮድ» እንዲሁም ከዚህ ምልክት ተወስዶ በዚያ መንገድ የዕብራይስጥና የአራማያ «ዮድ» የአረብኛም «ያእ» ወለደ። ከዚህ በላይ የግሪክ አልፋቤት «ኢዮታ» (Ι, ι) አባት ሆነ። እሱም የላቲን አልፋቤት (I i) እና (J j) ወላጅ ሆነ። ስለዚህ እነዚህ ሁሉ የ«የመን» ሩቅ ዘመዶች ሊባሉ ይቻላል። በተጨማሪ የግዕዝ ቁጥር (አሥር) ከግሪኩ ι በመወሰዱ እሱም የ«የ» ዘመድ ነው።