ወ ዉ ዊ ዋ ዌ ው ዎ



አቡጊዳ ታሪክ

ዋዌ (ወይም ዋውወዌ) በአቡጊዳ ተራ ስድስተኛው ፊደል ነው። እንዲሁም በከነዓንአራማያዕብራይስጥና በሶርያ ፊደሎች ስድስተኛው ፊደል «ዋው» ይባላል። በዓረብኛ ደግሞ «ዋው» በ«አብጃድ» ተራ 6ኛ ነው። (በዘመናዊ ተራ ግን 27ኛው ነው።)

በዘመናዊ ዕብራይስጥ «ዋው» (ו) ተናባቢ ሲሆን እንደ «ቭ» ይሰማል። አናባቢ ሲሆን ግን «ኡ» ወይም «ኦ» ያመለክታል።

ታሪክ ለማስተካከል

ተመሳሳይ ግብፃዊ ስዕል ቅድመ-ሴማዊ ሣባ ግዕዝ
T3
   


የዋዌ መነሻ ከቅድመ-ሴማዊ ጽሕፈት እንደ ሆነ ይታስባል። በዚህ ጽሕፈት ፊደሉ የበትር ስዕል መስለ። ለዚህም ተመሳሳይ የግብጽ ሀይሮግሊፍ «ሐጅ» ነበር።

ከነዓን አራማያ ዕብራይስጥ ሶርያ ዓረብኛ
    ו   و


የከነዓን «ዋው» እንዲሁም ከዚህ ምልክት ተወስዶ በዚያ መንገድ የዕብራይስጥና የአራማያ የአረብኛም «ዋው» ወለደ።

ከዚህ በላይ የከነዓን «ዋው» የግሪክ አልፋቤት «ዲጋማ» («ዋው») (Ϝ ϝ) አባት ሆነ፤ የ«ው» ድምጽ ግን ቀድሞ ከቋንቋው ጠፍቶ ዲጋማ እንደ ቁጥር ብቻ ጠቀመ። (ደግሞ ስቲግማ ይዩ።) በላቲን አልፋቤት ግን (F f) ከዲጋማ ተነሣ።

በኋላ ዘመን የከነዓን «ዋው» እንደገና የግሪክ «ኡፕሲሎን» (Υ υ) ወለደ። ይህም የላቲን አልፋቤት (V v) እና (Y y) እና የቂርሎስ አልፋቤት (У, у) ወላጅ ሆነ። እንደገና የላቲን ፊደሎች (U u) እና (W w) ከ«V» ስለተነሡ እነዚህ ሁሉ የ«ዋዌ» ሩቅ ዘመዶች ሊባሉ ይቻላል።