አምባሰልደቡብ ወሎ ዞን የሚገኝ ወረዳ ሲሆን ስሙ በዚህ ወረዳ ውስጥ ከሚገኝ አምባ ስም ይመነጫል። አምባሰል ወረዳ፣ በደቡብ ምዕራብ የባሽሎ ወንዝ ከጠንታ ወረዳ ሲለየው፣ በደቡብ የባሽሎ ገባሪ የሆነው ወላኖ ወንዝ ከኩታበር፣ እንዲሁ የ ሚሌ ወንዝ ደግሞ በስተ ደቡብ ምስራቅ ከተሁለደረ ወረዳ ይለየዋል። 44% የሚሆነው የወረዳው ክፍል ተራራማ፣ 36% ወጣ ገባ፣ 12% ገደላማ ሲሆን 7.5% ብቻ ለጥ ያለ ሜዳ ነው። ስለሆነም በዚህ ወረዳ አራት አይነት የአየር ንብረቶች ይገኛሉ፦ ውርጭደጋወይና ደጋ እና ቆላ፣ እያንዳንዳቸው .47%፣ 29.53%፣ 49.64%፣ 20.36% ይይዛሉ። የዚህ ወረዳ ታላቁ ከተማ ውጫሌ ሲሆን በአካባቢው በሚገኝ የተፈጥሮ ከሰል ክምችት ይታወቃል። የኢጣሊያ ወራሪ ሃይል ይህን የከሰል ክምችት አገር እስከለቀቀበት ዘመን ድረስ ይጠቀም ነበር[1]

አምባሰል
ውጫሌ ተራራ
ከፍታ 3567 ሜትር (አምባሰል ተራራ)
የሕዝብ ብዛት
   • አጠቃላይ 121,899
አምባሰል is located in ኢትዮጵያ
{{{alt}}}
አምባሰል

11°45′ ሰሜን ኬክሮስ እና 39°15′ ምሥራቅ ኬንትሮስ

ታሪክ ለማስተካከል

የዓፄ ይኩኖ አምላክ እናት ከሰገረት እንደመጣች ሲነገር፣ አባቱ ደግሞ ከዚህ ቦታ እንደመነጨ ይጠቀሳል። በዚህ ምክንያት ይመስላል፣ የዚህ አምባ ባለስልጣኖች ጃንጥራር በሚል ልዩ ማዕረግ ከጥንት ጀምሮ እስከ ንጉሳዊው ስርዓት ፍጻሜ አካባቢውን ያስተዳድሩ ነበር ( ከቅርብ ምሳሌ እቴጌ መነንጃንጥራር አስፋው ልጅ ነበሩ)። የይኩኖ አምላክ የልጅልጅ የሆኑት ዓፄ ጅን አሰገድ ተገዳዳሪ የነገሥታት ወንድ ልጆችን በዚህ ወረዳ በሚገኘው አምባ ግሸን ላይ ማሳሰር እንደጀመሩ ታሪክ ጸሐፊው ዋሊስ ባጅ ይጠቅሳል። እኒህ የሚታሰሩት ሰዎች ቤተ እስራኤል ወይንም በቀላሉ እስራኤላውያን ይባሉ ነበር። ስለሆነም ከአምባ ግሸን አጠገብ የሚገኘው ተራራ አምባ እስራኤል ወይንም አምባ ሰል መባል ጀመረ[2]

በ1682 ዓ.ም. የታተመው የቪቼንዞ ኮሮኔሊ ካርታ አምባ ሰልን በአምኅራ ግዛት የሚገኝ ተራራ እና የንጉሳዊ ቤተሰቦች መያዣ እንደሆነ ያሳያል[3]። ቆይቶ፣ የጣሊያን ወራሪዎች ከመምጣታቸው በፊት አምባሰል ከተራራ ስምነት ባሻገር የአስተዳደር ክፍል ስም በመሆን ከዋና ከተማው ማርየ ስላሴ ይተዳደር ነበር። በጣሊያን ወረራ ጊዜ የአምባሰል ዋና ከተማ ጎልቦ ሆነ፣ ለዚህም ምክንያቱ ለአዲስ አበባ - መቀሌ መንገድ ጎልቦ ስለሚቀርብ ነበር። ጣሊያኖች ሲባረሩ ዋና ከተማው ውጫሌ ተብሎ በወረዳነቱ ጸና። ቀጥሎ የአውርጃ ስርዓት ሲተገበር አምባሰል፣ ተሁለደረ እና ወረ ባቦ አንድ ላይ ሆነው የአምባሰል አውራጃን መሰረቱ። የአውራጃው ዋና ከተማ ሐይቅ ነበር። የደርግ ስርዓት በአውራጃነቱ ካስቀጠለው በኋላ የዞን ስርዓትን ሲተገብር አውራጃውን ወደ መሰረቱት ወረዳዎች በመክፍል አምባሰል በወረዳነቱ ጸና[4]። ወረዳው በአሁኑ ወቅት 23 ቀበሌዎችን አቅፎ ይገኛል። ይሄው ከበፊት ከነበረው 34 ጭቃዎች ዝቅ ያለ ነው።

ህዝብ ቆጠራ ለማስተካከል

የአምባሰል ሕዝብ ቁጥር [5][6]
ዓ.ም.** የሕዝብ ብዛት የተማሪዎች ብዛት
1986
111,172
1999
121,899


ማጣቀሻ ለማስተካከል

  1. ^ "Local History in Ethiopia" The Nordic Africa Institute website (accessed 15 February 2008)
  2. ^ Whiteway, R. S. (Richard Stephen), The Portuguese expedition to Abyssinia in 1541-1543 as narrated by Castanhoso, London, Printed for the Hakluyt Society, page ix,(1902) (በኢንተርኔት
  3. ^ የኢትዮጵያ ካርታ 1690
  4. ^ ኢንተርኔት
  5. ^ Census 2007 Tables: Amhara Region, Tables 2.1, 2.4, 2.5, 3.1, 3.2 and 3.4.
  6. ^ 1994 Population and Housing Census of Ethiopia: Results for Amhara Region, Vol. 1, part 1, Tables 2.1, 2.7, 2.10, 2.13, 2.17, Annex II.2 (accessed 9 April 2009)


አምባሰል አቀማመጥ
ዳውንትና ደላንታ ጉባ ላፍቶ ሐብሩ
ዳውንትና ደላንታ
 
አምባሰል
ወረባቦ
ጠንታ ኩታበር ተሁለደሬ