ሴቶች የሰው ልጆች አንስቶች ናቸው። እናቶቻችን፣ እኅቶቻችን፣ ሴት ልጃቸን ናቸው።

መካኒክ በኢትዮጵያ

«ሴት» የሚለው ቃል ወይም ስም ሌሎች ትርጉሞች አሉትና የተማሩ ሰዎች መለያየት አለባቸው። ከሰው ልጅ በቀር የማናቸውም እንስሳ ወይንም ተክል አንስታይ ብትሆን «ሴት እንስሳ» ወይም «ሴት ተክል» ልትባል ይችላል። ይህን በተመለከተ ሴት (ጾታ) የሚል መጣጥፍ አለ። በዘመናዊ አማርኛ የቃሉ «ሴት» ታሪክና መድረሻ ከግዕዝ ብእሲት (ሴት፣ ሚስት) ነበር። በድምጽ ለውጥ አጋጣሚ በቀድሞ ዘመን «ሴት» የወንድ ስም ነበር። በኦሪት ዘፍጥረትአዳምሔዋን ወንድ ልጅ ሴት ይባላል። የድምጽ ለውጥ አጋጣሚ ስለ ሆነ ከዘመናዊ «ሴት» (አንስት) ጋር ልዩ ግንኙነት የለውም፣ ባለፈውም ዘመን «ሴት» ለ«አንስት» እንዳላመለከተ ግልጽ ነው። እንዲሁም በጥንታዊ ግብጽ አረመኔ አፈ ታሪክ ሴት የተባለ ግለሠብ ወይም ጣኦት ይገኛል። ይህም እንደገና ከዘመናዊ «ሴት» (አንስት) ጋር ግንኙነት የለውም፣ ምናልባት ግን አፈ ታሪኩ ከአዳም ልጅ ሴት ጋር ሊዛመድ ይቻላል።

ለሴቶች (ብእሲት) አለም አቀፍ ምልክት አለ፣ ይህ ምልክት መስቀል ከክብ ነገር በታች ሲሆን የመስተዋት ምልክት እንዲወክል ነው። ይህም የፈለኩ ዘሃራ (ቬነስ) ምልክት ይባላል፣ በቀድሞ ጥንተ ንጥር ጥናት የመዳብም ምልክት ነበር።

በታሪክ ላይ ሴቶች እንደ ወንዶች የከበረ ሚና እና ከፍ ያለ ማዕረግ አገኝተዋል፣ በርካታ ንግሥቶች አገራቸውን በራሳቸው መብት ገዝተዋል። እንዲሁም ፕሬዚዳንቶች፣ ፋላስፎች፣ ጸሐፊዎች፣ ፈጠራ ፈልሳፊዎች፣ አስተማሪዎች፣ ሳይንቲስቶች፣ አትሌቶች፣ ገበሬዎች፣ ሆነዋል። ነቢዮችም ሆነዋል፣ ይህን የሚያስረዳ የነቢይቱ ዲቦራ ታሪክ ነው። ባጭሩ ወንድ የሚችል ሴት የማትችል ነገር፣ ወይንም ሴት የምትችል ወንድ የማይችል ነገር ጥቂት ብቻ ነው፣ እነዚህም በተለይ የማባዛት ሚናዎች (እንደ እርጉዝና) ናቸው።

በአንድ ቻይናዊ ምሳሌ «ወንዶችና ሴቶች አብረው ሰማይ እንዳይወድቅ ያንሳሉ።»

ባህል ጥናት ዘርፍ፣ የሴቶችና የወንዶች ሚናዎች ከባህል ወደ ባህል የሚለያዩ፣ አንዳንዴም በልማድ ወይም በሕጎች የሚወሰኑ ሆነዋል። እነዚህም ከወቅት ወደ ወቅት የሚለያዩ ሆነዋል።