ሱሙላኤል ከ1793 እስከ 1757 ዓክልበ. ድረስ (ኡልትራ አጭር) የባቢሎን ፪ኛ ንጉሥ ነበረ። አባቱን ሱሙ-አቡም ተከተለው።

ለዘመኑ 36 ያህል የዓመት ስሞቹ ታውቀዋል። ከነርሱም መካከል፦

1791 ዓክልበ. ግ. - «አሉምቢዩሙ (የካዛሉ ንጉሥ) በመሣርያዎች የተመታበት ዓመት»
1781 ዓክልበ. ግ. - «ኪሽ የጠፋበት ዓመት»
1776 ዓክልበ. ግ. - «ያህዚሬል ከካዛሉ የተባረረበት ዓመት»
1775 ዓክልበ. ግ. - «የኪሽ ግድግዳ የፈረሰበት ዓመት»
1774 ዓክልበ. ግ. - «የካዛሉ ግድግዳ የፈረሰበትና ሥራዊቱ በመሣርያዎች የተመታበት ዓመት»
1769 ዓክልበ. ግ. - «ያህዚሬል በመሣርያዎች የተመታበት ዓመት»

የሱሙላኤል ተከታይ ልጁ ሳቢዩም ነበረ።

ቀዳሚው
ሱሙ-አቡም
ባቢሎን ንጉሥ
1793-1757 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ሳቢዩም

የውጭ መያያዣ ለማስተካከል