1 ሪም-ሲን ከ1734 እስከ 1675 ዓክልበ. (ኡልትራ አጭሩ አቆጣጠር) የላርሳ መጨረሻ ንጉሥ ነበረ።

ሪም-ሲን በ1734 ዓክልበ. ወንድሙን ዋራድ-ሲንን በላርሳ ዙፋን ተከተለው። አባቱ ኤላማዊው-አሞራዊው አለቃ ኩዱር-ማቡግ ነበር።

በ1721 ዓክልበ. ጎረቤቶቹ ባቢሎንኡሩክራፒቁምኢሲን ላርሳን ለመቃወም በውል ተባበሩ። ሪም-ሲን ግን ሁላቸውን በአንድ ውግያ አሸነፋቸውና መንግሥቱን ያስፋፋ ጀመረ። በ1714 ዓክልበ. ኡሩክን ዘረፈ። በ1712 ግን የባቢሎን ንጉስ ሲን-ሙባሊት ድል አደረገው። በ1710 ዓክልበ. የኢሲንን ግዛት ወረረው፣ በ1705 ኢሲንን ከመጨረሻ ንጉሱ ከዳሚቅ-ኢሊሹ ያዘ። ይህም በሪም-ሲን መንግሥት በ30ኛው አመት ሆነ። ከዚህ ዓመት ጀምሮ የላርሳ ዓመታት ከኢሲን ውድቀት ጀምሮ ተቆጠሩ፤ ይህም አቆጣጠር እስከ ሪም-ሲን ዘመን መጨረሻ እስከ 1675 ዓክልበ. (= «31 ዓመት ኢሲን ከወደቀ») ተጠቀመ።

በ1699 የባቢሎን ንጉሥ ሃሙራቢ ኢሲንንና ኡሩክን ከሪም-ሲን ያዘ። (ሆኖም የላርሳ ዓመት ከኢሲን ውድቀት መቆጠር ያንጊዜ አልተወም።) በመጨረሻ በ1675 ዓክልበ. ሃሙራቢ ላርሳን ከበበው፤ ከ6 ወር በኋላ ላርሳ ለባቢሎን ወደቀ።[1]ይህም በሪም-ሲን 60ኛው ዘመነ መንግሥት ሆነ።

ቀዳሚው
ዋራድ-ሲን
ላርሳ ንጉሥ
1734-1675 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
የለም (ሃሙራቢ ላርሳን ያዘ።)

መጣቀሻዎች ለማስተካከል

  1. ^ History of the Ancient World, Susan Wise Bauer, W.W. Norton & Company, Inc., 2007, ISBN 978-0-393-05974-8

የውጭ መያያዣ ለማስተካከል