ሞጣ ከተማ የምትገኘው በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስትምስራቅ ጎጃም ዞን፣ በ ሁለት እጁ እነሴ ወረዳ ከአዲስ አበባ በ371 ኪሜ ከክልሉ መንግስት መቀመጫ ከሆነችው ባህርዳር ከተማ ደግሞ 120 ኪሜ ርቀት ላይ ከዞኑ መቀመጫ ከሆነችው ከደብረማርቆስ ደግሞ 192 ኪሎሜትር ርቀት ላይ ነው።


 አስትሮኖሚያዊ መገኛ ቦታዋ ደግሞ 11º 04’ ምስራቅ ላቲቲዩድ እና በ37º 52’ ሰሜን ሎንጊትዩድ ነው።

አመሰራረት ለማስተካከል

ሞጣ ከተማ የተቆረቆረችው በ 1747 ዓም ነው። የሞጣ ከተማ ስያሜን ስንመለከት ሁለት አይነት አመለካከቶች ይነሳሉ፡፡ የመጀመሪያው አመለካከት “አባ ሞፃ” ከሚባል መነኩሴ ስም የተወሰደ ነው የሚል ሲሆን ይኸውም መነኩሴ የሞጣ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ከመደበሩ በፊት የነበረና በቤተክርስቲያኑ የተቀበረ የመጀመሪያው ሰው ነው የሚል ነው፡፡ በብዛት ተቀባይነት ያለው አመለካከት ደግሞ የሞጣ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን አሰሪ ከሆነችው ከንግስት ምንትዋብ ልጅ ከልዕልት ወለተ እስራኤል ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ልዕልቲቱ ቤተክርስቲያን ማሰራት ትወድ ስለነበር አባቶች እሷ ከሞተች ማካካሻ ይሆናል ተብሎ የተሰጣት በመሆኑ ከዚያ የመጣ ስያሜ ነው ይላሉ፡፡ ልዕልት ወለተ እስራኤል የሞጣ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንን ከደበርሽ ከተማዋ ታድጋለች ያንች ህይወት ግን ያልፋል ነገር ግን መድሃኒያለም ቤተክርስቲያንን ከደበርሽ እድሜሽ ይረዝማል ከተማዋ ግን አታድግም የሚል ራዕይ አይታ ስለነበር ከተማዋ ብታድግና የእኔ ህይወት ቢያልፍ ይመረጣል በማለት የሞጣ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያንን ደበረች ከዚያም በኋላ ህይወቷ እንዳለፈና ከተማዋም ለእርሷ ማካካሻ እንዲሆን ተብሎ ከ1747 ዓ.ም ጀምሮ ስያሜዋን ያገኘች መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

ሞጣ ጊዮርጊስ

የህዝብ ብዛት ለማስተካከል

በ2005 ዓ.ም በማዕከላዊ የስታቲስቲክስ ባለስልጣን በተካሄደው የህዝብ ትንበያ መሰረት የከተማዋ ነዋሪ ህዝብ ብዛት 33,500 ነበር። ከዚህም ውስጥ 17060 (51%) ወንዶችና 16440 (49%) ሴቶች ናቸው፡፡


  1. ስዩም ይዘንጋው ድንቁ (talk) 14:24, 23 ጁላይ 2019 (UTC)