ዶ/ር ለገሠ ወልደዮሓንስ ለማስተካከል

ሺስቶሶሚያሲስ ወይም ቢልሃርዝያ (Bilharziasis) ሺስቶሶማ በሚባሉ የደም ወስፋቶች ደም ውስጥ መገኘት የሚመጣ የሰው በሽታ ነው። ወንድና ሴት ትሎች ተገናኝነው በመጣበቅ የሰው ደም ውስጥ በመኖር ብዙ ሺህ እንቁላሎች ያፈራሉ። እንቁላሎቻቸው ከሽንት ጋር ሲወጡም ደም ሊያሸኑ ይችላሉ። እንቅላሎቹ ከሰገራና ከሽንት ጋር ከሰውነት ወደ ውጪ ከወጡ በኋላ ተፈልፍለው ቀንድ ኣውጣ ውስጥ ገብተው ይራባሉ። ከእዚያም ከቀንድ ኣውጣው ወጥተው ውሃ ውስጥ በመቆየት የሰውን ቆዳ በስተው ወደ ደም ስር ይገባሉ። በሽታው ሰውን የሚይዘው ሰርኬርያ የሚባሉት የትሉ ኣንድ ዓይነት ደረጃ ሰው ሲዋኝ ወይም በባዶ እግሩ ውሃው ውስጥ ሲሄድ ቆዳን በመብሳት ወደ ሰውነት ስለሚገቡ ነው።

ዶ/ር አክሊሉ ለማ እንዶድ ቀንድ ኣውጣዎችን ለመግደል ስለሚችል በሽታውን ለመቆጣጠር እንደሚራዳ ስለደረሱበት ዕውቅና ተሰጥቷቸዋል። የእንዶድ ማዕክልም ኣቋቁመዋል። ስለ እንዶድ ምርምር ለብዙ ዓመታት በኣዲስ ኣበባ ዩኒቨርሲቲ ከዶ/ር ኣክሊሉ ጋር ስላደረጉት ኣስተዋጽዖ ዶ/ር ለገሠ ወልደዮሓንስ “ራይት ላይቭሊሁድ ኣዋርድ” ወይም “Right Livelihood Award” የሚባል ሽልማት በ፲፱፻፹፩ ዓ.ም. ተሰጥቷቸዋል። ዶ/ር ለገሠ በኦስሎ እና ኣዲስ ኣበባ ዩኒቭርሲቲዎችም ተሸልመዋል።

የውጭ መያያዣዎች ለማስተካከል