ሄርሚኖን (ወይም እርሚኖንሄርሚዮን) በጥንታዊ ጀርመናውያን ነገዶች መካከል አንዱ ዋና ክፍል ነበር። ስሙ በሮማውያን ታሪክ ጸሐፍት እንደ ታኪቱስፕሊኒ ዘንድ ይታወቃል።

ጀርማኒክ ቋንቋዎች 1 ዓ.ም. ግድም፣ ቢጫ፡- ኤልብ ወንዝ ጀርማኒክ ወይም «እርሚኖኒክ»

ፖምፖኒዩስ ሜላ (35 ዓ.ም.) እንዳለው፣ በባልቲክ ባህር ላይ ኪምብሪቴውቶኔስ ሲኖሩ ከነሱ ኋላ ሄርሚዮኔስ ከሁሉ በተራቀው ጌርማኒያ (ጀርመን) ክፍል ተገኙ።

ፕሊኒ (70 ዓ.ም. ግድም) እንደ ጻፈው፣ ጀመናውያን በ5 ንዑስ-ብሔሮች ተከፋፈሉ፤ እነርሱም ዋንዲሊ፣ ኢንግዋዮን፣ ኢስትዋዮን፣ ሄርሚዮን፣ እና ባስተርናይ ናቸው። በሄርሚዮን ነገዶች መካከል ስዌቢሄርሙንዱሪካቲ፣ እና ኬሩስኪ የተባሉ ጎሣዎች እንደ ኖሩ ይለናል።

ታኪቱስ (90 ዓ.ም.) እንደሚለን፣ በጀርመናውያን «ጥንታዊ ዘፈኖች» መሠረት በጥንት ማኑስ ሶስት ልጆች ነበሩት። እነኚህም 3 ልጆች ሦስት ንዑስ-ብሔሮች ወለዱ፦

በ820 ዓ.ም. ግድም ሂስቶሪያ ብሪቶኑም (የብሪታንያውያን ታሪክ) የሚባል መጽሐፍ ተጽፎ፣ የ«አላኑስ» ልጅ «አርሜኖን» ይባላል፤ አምስት ልጆቹም «ጎጡስ»፣ «ዋላጎጡስ»፣ «ኪቢዱስ»፣ «ቡርጉንዱስ»ና «ሎንጎባርዱስ» ሲሆኑ ከነዚህ ጎታውያን፣ ዋላጎታውያን፣ ጌፒዶችቡርጉንዳውያንሎንጎባርዳውያን እንደ ተወለዱ ይላል።

አኒዩስ ዴ ቪቴርቦ በ1490 ዓ.ም. ባሳተመው ጽሑፍ ዘንድ፣ ሄርሚዮን ከኢንጋይዎን ዘመን በኋላ በሳርማትያ ነገሠ፣ «በመሣርያዎች ሓይለኛ ሰው» ሲለው ሌላ መረጃ ስለርሱ አይሰጥም።

በ1513 ዓ.ም. ግድም ጀርመናዊው መምህር ዮሐንስ አቬንቲኑስ የጀርመን አገር ዜና መዋዕል አሳተመ። በዚህም ውስጥ እንደሚዘግበው፣ ሄርሚኖን የኢስቴዎን ልጅና ተከታይ ነው። ዋና ከተማው በሄርማንስሃይም (የአሁኑ ሬገንስቡርግ) ሆነ። በ764 ዓ.ም. የፍራንኮች ንጉሥ ካሮሉስ ማግኑስ ያጠፋው የአረመኔ ሐውልት «እርሚንሱል» በአቬንቲኑስ ዘንድ ሄርሚኖን ምኲራብ ያሠራበት ሥፍራ ነበር።

ሄርሚኖን የጦር ሠልፍ ትምህርት በጀርመን አገር አቆመ፣ በየአመቱም ብዙ ሺህ ወንዶች በግዴታ ወታደርነት ተመለመሉ ይለናል። በሄርሚኖን ዘመን አፒስግብጽ እንደ ነበር ይጨምራል። ሄርሚኖን ከነገሠ በኋላ ልጁ ማርሱስ በጀርመን ዙፋን ላይ ተከተለው ይላሉ።

ቀዳሚው
ኢስታይዎን
የቱዊስኮኔስ (ጀርመን) ንጉሥ
2092-2065 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ማርሱስ