ሀዳኒሽሱመራዊ ነገሥታት ዝርዝር ላይ የሐማዚ ንጉሥ ሲሆን ከኪሽ ነገሥታት በኋላና ከኡሩክ ንጉሥ ኤንሻኩሻና በፊት በሱመር ላዕላይነቱን ለ360 አመታት ያዘ። እንዲህ ረጅም ያለ ጊዜ እንደ ነገሠ ባይታስብም እንኳን ለጥቂት ዘመናት (ምናልባት 2243-2215 ዓክልበ. አካባቢ) በአገሩ እንደ ቆየ በቃላል ይቻላል። በሌላ ምንጮች በኩል ስሙ የሚገኝ በአንድ ሰነድ ብቻ አለ። ከብዙ መቶ ዘመን በኋላ የተጻፈ በኒፑር መቅደስ የነበሩት የባቢሎን ጣኦታት ዝርዝር እንደሚለው፣ በመቅደሱ በር ጎን ለጎን 2 የስፊንክስ ጣኦታት ስሞች «ሃታኒሽ እና ሉማ» ተባሉ። «ሉማ» ማለት የላጋሽ ንጉሥ ኤአናቱም ሌላ (አሞራዊ) ስም ነው፤ ደግሞ ሀዳኒሽ በኒፑርና ኪሽ እየገዛ ኤአናቱም በላጋሽ እንደ ነገሠ ይቻላል። የነገሥታት ዝርዝር ኤንሻኩሻና ከሀዳኒሽ የሱመር ላይኛነት እንደ ያዘ ሲል ኤንሻኩሻና እራሱ የኤአናቱም ተወዳዳሪ ሆነ።

ቀዳሚው
ኪሽ ንጉሥ ካልቡም
ሱመር (ኒፑር) አለቃ
2243-2215 ዓክልበ. ግድም
ተከታይ
ኡሩክ ንጉሥ ኤንሻኩሻና