ከ«ዒዛና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት
Content deleted Content added
No edit summary |
No edit summary |
||
መስመር፡ 1፦
'''ዒዛና''' (በ[[ግሪክ (ቋንቋ)|ግሪክ]]፡ '''ኤይዛናስ''')፣ ንጉሥ (ወደ 4ኛው ክ/ዘ አጋማሽ ዓ.ም)፣ ከ[[አክሱም]] ነገስታት ሁሉ ገናና የሆነ የመጀመሪያው ክርስትያን ንጉሥ። ምናልባት ለአባቱ ለንጉሥ [[ኢላ-አሚዳ]]፡ የበኩር ልጁ ሳይሆን አይቀርም። ስለ እናቱ ሥም የሚናገር [[ታዓማኒ]] የጽሑፍ መረጃ እስካሁን ድረስ አልተገኘም። ከሁለተኛ ደረጃ ምንጮች መሠረት ግን የእናቱ ሥም [[ሶፍያ]] ይባላል። ሁለቱ ወንድሞቹ [[ሣይዛና]] እና [[ኃደፋ]] በአስተዳደር እና በውትድርና ሥራዎች ይረዱት ነበር። በተለያዩ ጊዜያት ባደረጋቸው ተከታታይ የግዛት ማስፋፍያ ዘመቻዎች፡ ንጉሥ ዒዛና ግዛቱን በስሜን [[ቤጃ]]ዎች፣ [[ካሡ]]ና [[ኖባ]] በተባሉ የተከዘ ቀበሌዎች፣ በ[[አትባራ]] እና በ[[አባይ]] ወንዞች ፣ በምስራቅ በኩል በ[[አግወዛት]]፣ በደቡብ [[ስራኔ]] በተባለ የአፋን ምድሮች ላይ ወረራ እንደፈጸመ በ[[ግዕዝ]]፣ በጥንታዊ [[ዐረብኛ]]፣ እና በ[[ግሪክ]] ተጽፈው በ[[አክሱም]] የተገኙ የጽሑፍ መረጃዎች ያመለክታሉ። የግዛት ማስፋፍያ ዘመቻዎቹ ቅደም ተከተል ግን እስካሁን አከራካሪ ናቸው። ንጉሥ ዒዛና ከሚጠቀሱለት የአስተዳደር ባሕርያት ውስጥ፤ የተቀናቃኞችን እና የአመፀኞችን ግዛቶች ካስገበረ በኋላ በምሕረትና በበጎ አስተዳደር ሥርዓት መተካቱ ፣ የአመፀኞችን ኃይል ለመስበር የሚያደርጋቸው የርስት ነቀላና የተለዋጭ ሠፈራ እርምጃዎች ተጠቃሽ ናቸው። የዙፋኑ ሥያሜም፦ ዒዛና የአክሱም፣ [[ሒምያር]]፣ [[ራይዳን]]፣ [[ሳባ]]፣ [[ሳልሄን]]፣ [[ሲያሞ]]፣ [[ቤጋ]] ([[ቤጃ]]) እና [[ካሡ]] ንጉሥ። የደቡብ ዓረብያ ግዛቶች ሥም በዙፋኑ ሥያሜ መካተታቸው ከንጉሣዊ ራዕይ ወይም ምኞት የመነጩ እንጂ
በንጉሥ ዒዛና ዘመን፡ አክሱም በዓለም-ዓቀፍ ንግድ ረገድ እንደ ዝሆን ጥርስ፣ ወርቅ፣ የዔሊ ክዳን፣ ቆዳ፣ ቅመማ ቅመም ወዘተ ወደ ውጭ ትልክ እንደነበር፤ እንዲሁም ከወደ [[ሕንድ]] የሚመጡ ሽቀጦችን ከ[[ግሪኮች]]ና ከ[[ሮማዊያን]] ጋር የ[[አዱሊስ]] ወደብን በመጠቀም የንግድ ልውውጥ ያካሂዱ እንደነበር፣ በመዲናዋም የውጪ ዜጎች፣ ነጋዴዎች እና በልዩ ልዩ የሙያ መስኮች የተስማሩ በርካታ ነዋሪዎች ይኖሩባት እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ።
|