ከ«ዒዛና» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
አንዳንድ ማያያዣዎች ጨመርኩ ብቻ
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''ዒዛና''' (በ[[ግሪክ (ቋንቋ)|ግሪክ]]፡ '''ኤይዛናስ''')፣ ንጉሥ (ወደ 4ኛው ክ/ዘ አጋማሽ ዓ.ም)፣ ከ[[አክሱም]] ነገስታት ሁሉ ገናና የሆነ የመጀመሪያው ክርስትያን ንጉሥ። ምናልባት ለአባቱ ለንጉሥ [[ኢላ-አሚዳ]]፡ የበኩር ልጁ ሳይሆን አይቀርም። ስለ እናቱ ሥም የሚናገር [[ታዓማኒ]] የጽሑፍ መረጅ እስካሁን ድረስ አልተገኘም። ከሁለተኛ ደረጃ ምንጮች መሠረት ግን የእናቱ ሥም [[ሶፍያ]] ይባላል። ሁለቱ ወንድሞቹ [[ሣይዛና]] እና [[ኃደፋ]] በአስተዳደር እና በውትድርና ሥራዎች ይረዱት ነበር። በተለያዩ ጊዜያት ባደረጋቸው ተከታታይ የግዛት ማስፋፍያ ጦርነቶች፡ዘመቻዎች፡ ንጉሥ ዒዛና ግዛቱን በስሜን [[ቤጃ]]ዎች፣ [[ካሡ]]ና [[ኖባ]] በተባሉ የተከዘ ቀበሌዎች፣ በ[[አትባራ]] እና በ[[አባይ]] ወንዞች ፣ በምስራቅ በኩል በ[[አግወዛት]]፣ በደቡብ [[ስራኔ]] በተባለ የአፋን ምድሮች ላይ ወረራ እንደፈጸመ በ[[ግዕዝ]]፣ በጥንታዊ [[ዐረብኛ]]፣ እና በግሪክበ[[ግሪክ]] ተጽፈው በአክሱምበ[[አክሱም]] የተገኙ የጽሑፍ መረጃዎች ያመለክታሉ። የግዛት ማስፋፍያ ዘመቻዎቹ ቅደም ተከተል ግን እስካሁን አከራካሪ ናቸው። ንጉሥ ዒዛና ከሚጠቀሱለት የአስተዳደር ባሕርያት ውስጥ፤ የተቀናቃኞችን እና የአመፀኞችን ግዛቶች ካስገበረ በኋላ በምሕረትና በበጎ አስተዳደር ሥርዓት መተካቱ ፣ የአመፀኞችን ኃይል ለመስበር የሚያደርጋቸው የርስት ነቀላና የተለዋጭ ሠፈራ እርምጃዎች ተጠቃሽ ናቸው። የዙፋኑ ሥያሜም፦ ዒዛና የአክሱም፣ [[ሒምያር]]፣ [[ራይዳን]]፣ [[ሳባ]]፣ [[ሳልሄን]]፣ [[ሲያሞ]]፣ [[ቤጋ]] ([[ቤጃ]]) እና [[ካሡ]] ንጉሥ። የደቡብ ዓረብያ ግዛቶች ሥም በዙፋኑ ሥያሜ መካተታቸው ከንጉሣዊ ራዕይ ወይም ምኞት የመነጩ እንጂ በሐቅ ላይካተቱ ይችላሉ። ከወርቅ፣ ከብር እና ከነሓስ በተቀረጹት ገንዘቦቹ ላይ "ዒዛና ዘሐለን፣ የአክሱሞች ንጉስ" የሚል ጽሑፍ ይነበባል።
 
በንጉሥ ዒዛና ዘመን፡ አክሱም በዓለም-ዓቀፍ ንግድ ረገድ እንደ ዝሆን ጥርስ፣ ወርቅ፣ የዔሊ ክዳን፣ ቆዳ፣ ቅመማ ቅመም ወዘተ ወደ ውጭ ትልክ እንደነበር፤ እንዲሁም ከወደ ሕንድ የሚመጡ ሽቀጦችን ከግሪኮችና ከሮማዊያን ጋር የአዱሊስ ወደብን በመጠቀም የንግድ ልውውጥ ያካሂዱ እንደነበር፣ በመዲናዋም የውጪ ዜጎች፣ ነጋዴዎች እና በልዩ ልዩ የሙያ መስኮች የተስማሩ በርካታ ነዋሪዎች ይኖሩባት እንደነበር መረጃዎች ያመለክታሉ።
 
በንጉሥ ዒዛና ዘመን ዋንኛው ተጠቃሽ ክስተት ክርስትናን ከ[[ፍሬምናጦስ]] አምኖ መቀበሉ ነው። ሆኖም የክርስትና እምነት ወደ [[ኢትዮጵያ]] በ 4ኛው ክ/ዘ የመጀመሪያ ዓስርተ ዓመታት ውስጥ ቀደም ብሎ መግባት ጀምሮ ነበር። በቅድመ ክርስትና ዘመኑ፡ ንጉሥ ዒዛና [[አስቴር]]፣ [[መድር]]፣ [[ቤኄር]]፣ [[ሜኅረም]]፣ [[አረስ]] በተባሉ አማልክት ያምን እንደነበረና እራሱንም የነዚህ አማልክት ልጅ አድርጎ ይቆጥር እንደነበር በጽሑፍ የተገኙ መረጃዎች ያሳያሉ። በኋለኛ ዘመኖቹ ደግሞ የአሃዳዊ መለኮታዊ አምላክ አማኝ ስለመሆኑ የሚመስክሩ ጽሑፎች ተገኝተዋል። በ 1969 በተገኘ የመረጃ ሰነድ ላይ፡ ንጉሥ ዒዛና በግልፅ [[ክርስትያን]] ስለመሆኑ ሳያሻማ ይናገራል። በዘመኑ የተቀረፁት ሳንቲሞቹ ላይ የጨረቃና-ኮከብ የቅድመ ክርስትና ምልክቶች ቀስ በቀስ፡ የመስቀል ምልክቶች ባላቸው ሳንቲሞች እየተተኩ ሄደዋል። እንዲሁም የአርያኖች ንጉሥ [[ቆንስጣንጢኖስ]] (337-361) የላከው "ለተወደዱት ሁለት ወንድሞቼ ዒዛና እና ሳይዛና፡ የአክሱም ነገስታት" በማለት የሚጀምረው ታሪካዊ ደብዳቤ ስለ ፍሬምናጦስ ጵጵስና እና ዕውቅና ጉዳይ በሚመለከት ግለስቡን ወደ [[እስክንድርያ]] [[ፓትርያርክ]] [[አትናቴዎስ]] ዘንድ እንዲልኩት የሚጠይቀው ይህ ደብዳቤ እንደ ተጨማሪ መረጃ የሚያገለግል ስነድ ነው። ፍሬምናጦስን ከዚሁ ደብዳቤ መላክ ሃያ አምስት ዓመት ቀደም ብሎ በኢትዮጵያ ጳጳስ አድርጎ ሾሞ የላከው ይኸው ንጉስ አትናቴዎስ ነበር።
 
በነገስታት ዝርዝር ላይ የንጉሥ ዒዛና ሥም አለመታወቁ ያስገርማል። ሆኖም በሳንቲሞቹ ላይ ያለው ሥምይኸው "ዒዛና" የሚለው ነው ያለው። በዘልማድ እንደሚነገረው ግን፡ ንጉሥ አብርሃ እና ወንድሙ አጽብሃ ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ በገባበት ዘመን ኢትዮጵያን የሚገዙ ወንድማማች ንጉሦች ነበሩ። ምናልባት ክርስትናን በተቀበሉበት ጊዜ የወስዱት የክርስትና ሥማቸው ሊሆን ይችላል።
 
ስለ ንጉሥ ዒዛና ዘመነ ንግስ ፍፃሜ ወይም ስለ አሟሟቱ የሚዘረዝር ተጨባጭ መረጃ እስካሁን አልተገኘም። በአፈ-ታሪክ መረጃዎች መሠረት ግን ንጉሡ በምዕራብ ኢትዮጵያ አካባቢ በተደረገ ጦርነት በጀብድ ወድቆ እንደሞተ እና አስከሬኑም ወደ ምስራቅ ትግሬ መጥቶ እንደተቀበረ ይነገራል።
 
ምንጭ፦ ዲክሽነሪ ኦፍ ኢትዮጵያን ባዮግራፊ፣ ቮልዩም 1፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ጥናት ማዕከል፣ 1975 (በእንግሊዘኛ የታተመ)
 
ከ ወሂብ ባዩ
{{መዋቅር}}