ከ«ሀዲስ ዓለማየሁ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
«ሀዲስ ዓለማየሁ (ዶ/ር)» ወደ «ሀዲስ ዓለማየሁ» አዛወረ: የአርዕስትና የስም አጻጻፍ ልምድ‎ ይመልከቱ
No edit summary
መስመር፡ 1፦
[[Image:Haddis_alemayehu.jpg‎|thumb|right]]ደራሲ ዶ/ር '''ሀዲስ ዓለማየሁ''' ከአባታቸው ከቄስ ዓለማየሁ ሰለሞን እና ከእናታቸው ከወይዘሮ ደስታ ዓለሙ በ[[ደብረ ማርቆስ]] አውራጃ በጎዛመን ወረዳ በእንዳዶም ኪዳነ ምኅረት ቀበሌ በ[[ጥቅምት 5]] ቀን [[1903]] ዓ.ም. ተወለዱ። ገና በጨቅላ እድሜያቸው በቤተ ክርስቲያን የሚሰጠውን ትምህርት መከታተል ጀመሩ። የቤተክርስቲያን ስርዐታትንና መንፈሳዊ ትምህርትን በጎጃም ገዳማት በደብረ ኤልያስ፣ በደብረ ወርቅና በዲማ ከቀሰሙ በኋላ ወደ [[አዲስ አበባ]] በመሄድ በ[[ስዊድን]] ሚሽነሪ ትምህርት ቤት በኋላም በራስ [[ተፈሪ መኮንን ትምህርት ቤት]] ትምህርታቸውን ተከታተሉ። ለትንሽ ግዜ በአስተማሪነት ሥራ ተሰማርተው እንዳገለገሉ የፋሽስት [[ጣሊያን]] ወረራ ተከሰተ።
 
በጦር ሜዳ ዘምተው ሲዋጉ ቆይተው በአርበኝነት ሲንቀሳቀሱ በመያዛቸው ጣሊያን ከራስ [[እምሩ ኃይለ ሥላሴ]] ጋር ተልከው ለሰባት ዓመት በ[[ፖንዞ ደሴት]]ና በ[[ሊፓሪ ደሴት]] ታስረው ቆይተዋል።