ከ«ደጃዝማች ኪዳኔ ወልደመድኅን» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
[[Image:Kidane Aba Kesto.jpg|thumb|300px]]
 
'''ኪዳኔ ወልደመድኅን''' ዓርብ [[ሐምሌ 2]] ቀን [[1907]] ዓ.ም [[ቡልጋ]] በ[[ከሰም ወረዳ]]፤ [[የለጥ]] ቀበሌ፤ ልዩ ስሙ ቡሄ አምባ በሚባለው ሥፍራ ላይ ከናታቸው ከወይዘሮ አስካለ ደጀን እና ከአባታቸው ከቀኛዝማች ወልደመድኅን አዩደረስ ተወልደው [[ነሐሴ 10]] ቀን በጥምቀት ስም ኪዳነ ማርያም ተሰይመው [[የለጥ ቅዱስ ጊዮርጊስ]][[ ቤተ ክርስቲያን]] [[ክርስትና]] ተነሱ። አባታችው ቀኛዝማች ወልደመድኅን ትውልድ ሃገራቸው ወበሪ ሲሆን፤ በዘመኑ የታወቁ ስመጥሩ ጠበቃ ነበሩ። ከወይዘሮ አስካለም ጋር የተገናኙት ሁለቱም እወረዳው ፍርድ ቤት [[ኮረማሽ]] ለየጉዳያቸው ሄደው እንደነበር ይነገራል። ኪዳነማርያምም እስከ 7 ዓመት እድሜያቸው እዚያው ቡሄ አምባ ከአያታቸው አቶ ደጀን ደብሩ ቤት እንዳደጉና የቄስ ትምህርት ቤት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን እንደተከታተሉ ተጽፏል። ከዚህ በኋላ አባታቸው ቤት እያደጉ የ[[አማርኛ]]ና የ[[ግእዝ]] ትምህርት አጠናቀዋል።
 
አካለ መጠን ሲደርሱ በ18 ዓመታቸው በ[[1925]] ዓ.ም. [[አዲስ አበባ]] በ[[ክብር ዘበኛ]] ደንብ ተቀጥረው ወዲያው በ[[ቀኅሥ|ንጉሠ ነገሥቱ]] ትዕዛዝ ከ69 አዲስ ወታደሮች ጋር [[ባሌ]] ተመድበው እስከ [[1927]] ዓ.ም ድረስ በተራ ወታደርነት ከዚያም በ ሃምሳ ዓለቃና በባሻነት ማእረግ ሲያገለግሉ ከቆዩ በኋላ [[ጣሊያን]] [[ኢትዮጵያ]]ን ሊወር ሲመጣ በ[[1928]] ዓ.ም በምስራቅ ደቡብ በ[[ደጃዝማች በየነ መርዕድ]] እና በ[[ጄነራል አስፋው ወልደ ጊዮርጊስ]] መሪነት፤ የመጀመሪያ ልጃቸው ዓለማየሁ በተወለደ በዘጠኝ ቀኑ፤ [[ጥቅምት 11]] ቀን [[1928]] ዓ.ም ከጎባ ወደ [[ኦጋዴን]] ዘመቱ።