ከ«ኤንመርካር» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''ኤንመርካር''' በ[[ሳንጋር]] (ሱመር) ነገስታት ዝርዝር ዘንድ [[ኡሩክ]] (ኦሬክ) ከተማ የመሰረተ ነበር፤ በዚያ ዝርዝር ጽህፈት 420 ዓመት እንደ ነገሰ ይላል። ደግሞ አባቱ የ[[ኡቱ]] ልጅ [[መስኪያግካሸር]] ወደ ባሕር ገብቶ ኤንመርካር መንግስቱን ከ[[ኤያና]] ከተማ እንዳመጣ ይጨምራል።
 
ኤንመርካር ካንዳንድ ሌሎች የሳንጋር አፈታሪክ ይታወቃል፤ በተለይም የሰው ልጅ ልሳናት መደባለቅ የሚናግር [[ኤንመርካርና የአራታ ንጉስ]] በተባለው ተረት ራሱ የኡቱ ልጅ ይባላል። ኡቱ በሳንጋር እምነት የ[[ጸሓይ]] አምላክ ነበር። ኡሩክ ከመመስረቱ በላይ ታላቅ መስጊድ በ[[ኤሪዱ]] እንዳሰራ ይተረታል።
 
[[ዴቪድ ሮኅል]] የሚባል አንድ የታሪክ ሊቅ የኤንመርካርና የ[[ናምሩድ]] ተመሳሳይነት አመልክቷል። "-ካር" የሚለው ክፍለ-ቃል በሳንጋር ቋንቋ ማለት "አዳኝ" ሆኖ ኡሩክ የተመሠረተ በኤንመር-ካር ሲሆን፣ ደግሞ ናምሩድ፣ አዳኝ፣ በ[[ኦሪት ዘፍጥረት]] ምእራፍ 10 ዘንድ ኦሬክን ሰራ። በብዙ አፈታሪኮች ደግሞ ናምሩድ የ[[ባቢሎን ግንብ]] መሪ የሆነ ነበር። በተጨማሪ ሮህል የኤሪዱ መጀመርያ ስም "ባቤል" እንደ ነበር ያስባል፤ እዚያም የሚገኘው የግንብ ፍረስራሽ የባቢሎን ግንብ ፍርስራሽ መሆኑን ገመተ።