ከ«አቡጊዳ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
'''አቡጊዳ''' ማለት ፊደል ነው። ከ[[ልሳነ ግእዝ]] የተነሣ ነው። ቢሆነምቢሆንም በቅርብ ጊዜ አንዳንድ የፈረንጅ አገር ሊቅ ይህን አባባል ለቋንቋዎች ጥናት ተበድሯል። በዚሁ አነጋገር "አቡጊዳ" ማለት በዓለም የሚገኙ ብዙ አይነት ጽሕፈቶች ሊያመለክት ይችላል። በየአገሮቹ ፊደላቸው "አቡጊዳ" የሚባለው እያንዳንዱ ፊደል ለክፍለ-ቃል ለመወከል ሲሆን ነው እንጂ እንደ [[እንግሊዝኛ]] "አልፋቤት" ፊደሉ ለ1 ተነባቢ ወይም ለ1 አናባቢ ብቻ ሲሆን አይደለም። ስለዚህ የግዕዙ ፊደል ይሁንና ሌሎችም ለምሳሌ ብዙ የ[[ህንድ]] አገር አጻጻፎች ደግሞ አቡጊዳ በሚለው ስም ይታወቃሉ።
 
''[[ብራህሚክ]]'' ወይም ''[[ደቫናጋሪ]]'' በተባሉ የህንድ አጻጻፎች በኩል እያንዳንዱ ክፍለ-ቃል በተለየ ፊደል ሲወከል የአናባቢዎች መጠን የሚታየው የፊደሉን መልክ (እንደ ግዕዝ ወይም እንዳማርኛእንደ አማርኛ) ትንሽ በመቀየሩ ይሆናል። ስለዚህ በቋንቋ ሊቃውንት ዘንድ አቡጊዳዎች ይባላሉ። በተጨማሪ፣ በ[[ካናዳ]] አገር ለ[[የካናዳ ጥንታዊ ኗሪዎች|ጥንታዊ ኗሪ]] ([[ኢንዲያን]] የተባሉ) ጐሣዎች ያላቸው አጻጻፍ እንደዚህ አይነት ነው፤ አናባቢው የሚታየው ፊደሉን በመዞር ወይም በመገልበጥ ነውና።
 
በግእዝ አቡጊዳ ለሚለው የቃሉ መነሻ ከ[[ግሪክ|ግሪኩ]] ፊደል ተራ የሚለቀመው ነበር። በግሪኩ ይህ ፊደል ተራ በ '''A, Β, Γ, Δ''' ጀመረ፤ ወይም በስም ''አልፋ፣ ቤታ፣ ጋማ፣ ዴልታ'' ናቸው። ይህ ፊደል ተራ በ ሀ ሁ ሂ ሃ በሚል ቅርጽ ማለት በግእዝ፣ በካዕብ፣ በሣልስ፣ በራብእ ውስጥ ገብቶ ሲሰካ፣ አ፣ ቡ፣ ጊ፣ ዳ የሚለውን ፊደል ተራ አስገኘ። ሁሉ በሙሉ የግእዝ አቡጊዳ እንግዲህ እንደሚከተለው ሰንጠረዥ ነው።