ከ«ሚስቶች በኖህ መርከብ ላይ» ለውጦች መካከል ያለው ልዩነት

Content deleted Content added
No edit summary
No edit summary
መስመር፡ 1፦
ከ[[ማየ አይህ]] በፊት በነበሩ ዕለታት ስለ ኖሩ በ[[ኖህ]] መርከብ ላይ ስለ ተገኙ ስለ አራቱ ሴቶች [[ኦሪት ዘፍጥረት]] ምንም እንኳን ዝም ቢል፣ ከሌላ ምንጭ ስለነዚሁ ሴቶችና በተለይ ስለ ስሞቻቸው የተገኘው [[አፈ ታሪክ]] በርካታ ነው።
 
በጥንታውያን እምነት ዘንድ፣ የ[[ሴም]]፣ የ[[ካም]]ና የ[[ያፌት]] ሚስቶች ዕጅግ የረዘማቸው ዕድሜ ሲኖራቸው ከመጠን ይልቅ ለብዙ መቶ ዓመታት ኑረው ለያንዳንዱ ትውልድ ትንቢት እየተናገሩ ኖሩ። እነኚህ [[ሲቡሎች]] ተብለው ለ[[ግሪኮች]] ለ[[ሮማውያን]]ም እንደ ቅዱሳን ምጻሕፍት የተቆጠሩ የ[[ሲቡላውያን ንግሮች]] የተባሉት ሰነዶች ደራሲዎች የነበሩ እነሱ ናቸው። ከነሱም በኋላ ሌሎች ሲቡሎች ደግሞ እንደ ተከተሉ ለንግሮቹም እንደ ጨመሩ ይታስባል።
መስመር፡ 12፦
በኋላ ዘመን የክርስቲያን ጸሓፊ [[ቅዱስ አቡሊድስ]] (235 ዓ.ም. የሞቱ) በ[[ሶርያ ታርጉም]] ዘንድ ለዚህ ተመሳሳይ የሆነ ታሪክ አወሩ። ነገር ግን የሴምና የካም ሚስቶች ስሞች እንዳለዋወጡ ይመስላል። እሱ እንዲሁ "የኖህ ልጆች ሚስቶች ስሞች አንዲሁ ናቸው፤ የሴም ሚስት፣ '''ናሃላጥ ማህኑክ'''፤ የካምም ሚስት፣ '''ዘድካት ናቡ'''፣ የያፈትም ሚስት '''አራጥካ''' ይባላሉ" ብሎ ጻፈ።
 
[[ጆን ጊል]] (1697-1771 እ.ኤ.አ.) በመጽሓፍ ቅድስ ነክ አስተያይቶቹ ስለ አንድ የ[[ዓረብ]] [[አፈ ታሪክ]] የጻፈው እንዲሁ ነው፤ "የሴም ሚስት ስም '''ዛልበጥ''' ወይም '''ዛሊጥ''' ወይም '''ሳሊት'''ሲሆን፣ የካምም ድግሞ '''ናሓላጥ''' ተባለች፣ የያፌትም ደግሞ '''አረሢሢያ''' ተባለች።
 
በሲቡላውያን ንግሮች ዘንድ፣ ከሲቡሎቹ የአንዲቱ ስም ለ'''ዛልበጥ''' ተመሳሳይ ነበረች፤ እሷም የ"ባቢሎን ሲቡል" '''ሳምበጥ''' ነበረች። ከጥፋት ውሃ 900 አመት በኋላ ወደ ግሪክ አገር ሄዳ የንግሮች ጽሑፍ እንደ ጀመረች ብላ ጻፍች። ከዚያ በላይ የጻፈችው ጽሁፍ ከማየ አይህ አስቅድመው የኖሩት የቤተሠቧ ስሞች ይታርካሉ። እነሱም አባቷ ''ግኖስቲስ''፣ እናቷ ''ኪርኬ''፤ እህቷም ''ዒሲስ'' ናቸው።